ጽድቁን (Tsedqun) - ዮሐንስ ፡ በላይ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ በላይ
(Yohannes Belay)

Yohannes Belay 3.jpg


(3)

ጽድቁን
(Tsedqun)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ በላይ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Belay)

አምላኬን ፡ ልፈልግ ፡ በጠዋት ፡ በማታ (፪x)
ጽድቁን ፡ ብቻ ፡ ልራብ ፡ መሽቶም ፡ እስኪነጋ (፪x)
አምላኬን ፡ ልፈልግ ፡ በጠዋት ፡ በማታ (፪x)
ጽድቁን ፡ ብቻ ፡ ልራብ ፡ መሽቶም ፡ እስኪነጋ (፪x)

ጽድቁን ፡ ነው ፡ ዛሬም ፡ እራቤ
ጽድቁን ፡ ነው ፡ ነገም ፡ ጥማቴ
ጽድቁን ፡ ነው ፡ ሁሌም/ዛሬም ፡ እረሃቤ
የምድሩ ፡ ትርፍ ፡ ነው ፡ ለእኔ (፪x)

በጉብዝናህ ፡ ወራት ፡ ፈጣሪን ፡ ማሰብ
ይሻል ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ነገር
ይሄ ፡ ሚስጥር ፡ ገብቶኝ ፡ የምድሩን ፡ ንቄያለሁ
ክብርህን ፡ ሳይ ፡ ብቻ ፡ እኔስ ፡ እጠግባለሁ

በጉብዝናህ ፡ ወራት ፡ ፈጣሪን ፡ ማሰብ
ይሻል ፡ አይደለም ፡ ወይ ፡ ከዚህ ፡ ዓለም ፡ ነገር
ይሄ ፡ ሚስጥር ፡ ገብቶኝ ፡ የምድሩን ፡ ንቄያለሁ
ጽድቁን ፡ ብቻ ፡ ሳስብ ፡ እኔስ ፡ እጠግባለሁ

አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ
አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ

ስለምድር ፡ ሳስብ ፡ ለሚያልፈው ፡ ስጨነቅ
ዓመታት ፡ አለፉ ፡ ብዙ ፡ ለፋሁ ፡ ደከምኩ
አሁን ፡ በልጦብኛል ፡ የላዩ ፡ ተስፋዬ
አይረባኝም ፡ አወቅኩ ፡ የምድሩን ፡ መቆፈሬ (፪x)

አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ
አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ

አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ
አይበልጥም ፡ ወይ (፬x) ፡ ጌታ ፡ አይሻልም ፡ ወይ