From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
እግዚአብሔር ቸር አምላክ ነው
ያለህ በምህረት ተሞልተህ
እግዚአብሔር ደግ አምላክ ነው
ያለህ በምህረት ተሞልተህ
አንተ ፃድቅ ነህ
አንተ አዋቂ ነህ
አንተ መልካም ነህ
አንተ ትክክል ነህ
ተመስገን/8
ደርሶ በከበበን በጠላት ሃይል ላይ
በምስጋና አጊጠን ስትወድ እንድንታይ
ጦር ይዞ ፊታችን ለተሰለፈብን
እንድንዘምርልህ በገናን ስትሰጠን
አንትኮ ፃድቅ ነህ
አንተ አዋቂ ነህ
አንተ መልካም ነህ
አንተ ትክክል ነህ
እንዴት እንደምታድን ታውቃለህ
በስራህ ትታመናለህ
ምን እንደምታደርግ ታውቃለህ
ለቃልህ ታማኝ አምላክ ነህ
ትላንት ቅይ ባህርን ከፍለህ ያሻገርከውን
በደረቅ አራምደህ ያሻለፍከውን ህዝብህን
ዛሬ ላይ ዮርዳኖስ ያለወትሮው ሞልቶ
በሉ እርገጡት ስትል ከ አፍህ ቃል ወቶ
አንትኮ ፃድቅ ነህ
አንተ አዋቂ ነህ
አንተ መልካም ነህ
አንተ ትክክል ነህ
እንዴት እንደምታድን ታውቃለህ
በስራህ ትታመናለህ
ምን እንደምታደርግ ታውቃለህ
ለቃልህ ታማኝ አምላክ ነህ
ተመስገን/8
|