Yidnekachew Teka/Eyesus/13

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የማይታለፍ ፡ ይመስል ፡ ነበር ግን ፡ አሳለፈኝ ፡ አምላኬ ፡ እግዚአብሔር ክብሩ ፡ እንደ ፡ ጋሻ ፡ ሆኖ ፡ ከለለኝ የዜማ ፡ ጊዜ ፡ ለኔስ ፡ በዛልኝ

የኔ ፡ ሞገስ ፡ አየጨመረ የኔ ፡ ሕይወት ፡ እየደመቀ የኔ ፡ ነገር ፡ እየበረታ የኔ ፡ ሰላም ፡ በዛ ፡ በጌታ (፪x)

የኔ (የኔ ፡ የኔ) የኔ ፡ ሞገስ (እየጨመረ) የኔ ፡ ሕይወት (እየደመቀ) የኔ ፡ ሰላም (እየጨመረ) (፪x)

ላልሰማው ፡ አሰማ ፡ አለብኝ ፡ ልቤ ፡ ይሄ ፡ ልቤ አትሄድም ፡ ለሚልህ ፡ ተናገር ፡ አለኝ ፡ በል ፡ አለኝ

ሌላ ፡ ሌላ ፡ ቃል ፡ አለ ፡ ትሄዳለህ (እኔን ፡ ያለ) ሌላ ፡ ሌላ ፡ ቃል ፡ አለ ፡ ትሄዳለህ (እኔን ፡ ያለ) ሌላ ፡ ሌላ ፡ ድምፅ ፡ አለ ፡ ክብር ፡ አለ (እኔን ፡ ያለ) ኧረ ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ድምፅ ፡ አለ ፡ ሞገስ ፡ አለ (እኔን ፡ ያለ)

እኔን ፡ ያለ እኔን ፡ ያለ እኔን ፡ ያለ እኔን ፡ ያለ እኔን ፡ ያለ እኔን ፡ ያለ

ትሄዳለህ (እኔን ፡ ያለ) ክብር ፡ አለ (እኔን ፡ ያለ) ሞገስ ፡ አለ (እኔን ፡ ያለ) ትበዛለህ (እኔን ፡ ያለ)

የእሳት ፡ ቅጥር ፡ ነው ፡ በዙሪያዬ ፡ አሆ በውስጤ ፡ ክብር ፡ ነው ፡ ጌታዬ ፡ አሆ ጠላት ፡ ሊገፋኝ ፡ ሲሞክር ፡ አህህ ፡ ሲሞክር ራሱ ፡ ወደቀ ፡ እግሬ ፡ ስር

የቀኙ ፡ ግርማ ፡ የክንዱ ፡ ክብር አለ ፡ ከኔ ፡ ጋር ፡ አጥሮት ፡ ዙሪያዬን ሊቀርብ ፡ አልቻለም ፡ ጠላቴ ፡ ደፍሮ ክብሩ ፡ ስላለ ፡ እንዴት ፡ ተብሎ

አይሰማም ፡ ለቅሶ ፡ ቤቴ አስቆኛል ፡ አንዴ ፡ አባቴ ጠላቶቼ ፡ ለቅሶ ፡ ሲሹ ሳቄን ፡ ሰምተው ፡ ወዲያው ፡ ሸሹ ወዲያው ፡ ሸሹ

ባረከና ፡ በራረከኝ ታላቅነት ፡ ጨመረብኝ አገኘና ፡ ብቻዬን እንዲህ ፡ አለኝ ሀገር ፡ ነህ ፡ ሀገር ፡ ነህ ሕዝብ ፡ ነህ ፡ ሕዝብ ፡ ነህ

(አሆ) እኔን ፡ ያለ (አሆ) እኔን ፡ ያለ (አሆ) በዙሪያዬ (አሆ) የእሳት ፡ ቅጥር (አሆ) ሆኖልኛል (አሆ) ውስጤም ፡ ክብር (፪x)

አልሰራብኝም ፡ የእርሱ ፡ መርዶ ፡ አሆ አባት ፡ እግዚአብሔር ፡ ወዴት ፡ ሄዶ ፡ አሆ ተጠብቆልኝ ፡ ቀን ፡ ለሊቴ ፡ አህህ ፡ ቀን ፡ ለሊቴ ወደኔ ፡ አይቀርብም ፡ ያ ፡ ጠላቴ

የዜማ ፡ ዕቃዬ ፡ ይነሳ ፡ ለእርሱ ቅኔው ፡ ይደርደር ፡ ይክበር ፡ ንጉሱ በአጠገቤ ፡ ሺህ ፡ በቀኜ ፡ አስር ፡ ሺህ ጣልኩኝ ፡ በስሙ ፡ ሆንኩኝ ፡ ድል ፡ ነሺ

አይሰማም ፡ ለቅሶ ፡ ቤቴ አስቆኛል ፡ አንዴ ፡ አባቴ ጠላቶቼ ፡ ለቅሶ ፡ ሲሹ ሳቄን ፡ ሰምተው ፡ ወዲያው ፡ ሸሹ ወዲያው ፡ ሸሹ

ባረከና ፡ በራረከኝ ታላቅነት ፡ ጨመረብኝ አገኘና ፡ ብቻዬን እንዲህ ፡ አለኝ ሀገር ፡ ነህ ፡ ሀገር ፡ ነህ ሕዝብ ፡ ነህ ፡ ሕዝብ ፡ ነህ

(አሆ) እኔን ፡ ያለ (አሆ) እኔን ፡ ያለ (አሆ) በዙሪያዬ (አሆ) የእሳት ፡ ቅጥር (አሆ) ሆኖልኛል (አሆ) ውስጤም ፡ ክብር (፪x)