እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (Endiet Endiyaden Yawqal Egziabhier) - ወርቅነህ ፡ አላሮ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ወርቅነህ ፡ አላሮ
(Workneh Alaro)

Workneh Alaro 1.jpg


(1)

ከእሳት ፡ ውስጥ ፡ የነጠቀኝ
(Kesat West Yeneteqegn)

ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የወርቅነህ ፡ አላሮ ፡ አልበሞች
(Albums by Workneh Alaro)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
የሚያመልኩትን ፡ የእርሱ ፡ የሆኑትን
በፈተና ፡ ሆነው ፡ የሚያለቅሱትን (፪x)

አመጻ ፡ ቢጀመር ፡ ምናምንቴ ፡ በዝቶ
ጻድቅ ፡ ቢከበብ ፡ ጠላት ፡ አንሰራርቶ
በአመጸኞች ፡ ኑሮ ፡ ያን ፡ የተገፋውን
ሊያድን ፡ ይመጣል ፡ እግዚአብሔር ፡ ባሪያውን
(፪x)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
የሚያመልኩትን ፡ የእርሱ ፡ የሆኑትን
በፈተና ፡ ሆነው ፡ የሚያለቅሱትን (፪x)

ድብልቅ ፡ ህዝብ ፡ ነው ፡ በግብጽ ፡ የወጣው
የእግዚአብሔርን ፡ ወገን ፡ መለየት ፡ ከባድ ፡ ነው
ቢሆንም ፡ አምላኬ ፡ የእርሱ ፡ የሆኑትን ፡ ያውቃል
ማውረስ ፡ ያለበትን ፡ ትውልድ ፡ ያሻግራል
(፪x)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
የሚያመልኩትን ፡ የእርሱ ፡ የሆኑትን
በፈተና ፡ ሆነው ፡ የሚያለቅሱትን (፪x)

እግዚአብሔር ፡ ባርያውን ፡ ማንም ፡ አይጐዳም
ከእሳት ፡ ውስጥ ፡ ሲመጣ ፡ ያኔ ፡ ምልክት ፡ አያልፍም
የማምለጫ ፡ አለት ፡ ነው ፡ በእርግጥ ፡ ያስመልጣል
በእርሱ ፡ ያመነን ፡ መቼ ፡ ያሳፍራል
(፪x)

አዝ፦ እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያድን ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
እንዴት ፡ እንዲያስመልጥ ፡ ያውቃል ፡ እግዚአብሔር (፪x)
የሚያመልኩትን ፡ የእርሱ ፡ የሆኑትን
በፈተና ፡ ሆነው ፡ የሚያለቅሱትን (፪x)