መድኃኒቴ (Medhanitie) - ትዕግሥት ፡ ዓለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ትዕግሥት ፡ ዓለሙ
(Tigist Alemu)

Lyrics.jpg


(1)

ማራናታ
(Maranatha)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2006)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 3:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የትዕግሥት ፡ ዓለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Tigist Alemu)

እጅግ ፡ ከሚያስፈራው ፡ ከገሃነም ፡ እሳት
መድሃኒት ፡ የሆንከኝ ፡ ነፍሴን ፡ የታደካት
ወደ ፡ ውስጤ ፡ ገብተህ ፡ ፈውስን ፡ አግኝቻለሁ
ለዘለዓለሙ ፡ ሳልሰጋ ፡እኖራለሁ (፪x)

አዝ፦ መድሃኒቴ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ኦሆሆ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም ፡ አሃሃ
እውነተኛ ፡ አዳኝ ፡ ኦሆሆ ፡ ፈዋሽ ፡ የሆንከኝ ፡ አሃሃ
ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም (፪x)
ሃሌሉያ

መከራ ፡ ዙሪያዬን ፡ ሲያስፈራ ፡ ሲከበኝ
ቀር ቦ ፡ የነበረ ፡ ወዳጅም ፡ ሲሸሸኝ
ያለኝ ፡ የመሰለኝ ፡ ከጄ ፡ ሲጠፋብኝ
አልጥልሽም ፡ እኔ ፡ ከአንቺ ፡ ጋር ፡ ነኝ ፡ አልከኝ (፪x)

አዝ፦ መድሃኒቴ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ኦሆሆ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም ፡ አሃሃ
እውነተኛ ፡ አዳኝ ፡ ኦሆሆ ፡ ረዳት ፡ የሆንከኝ ፡ አሃሃ
ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም (፪x)
ሃሌሉያ

ዛሬም ፡ ወደፊት ፡ ለሚያስፈልገኝ
ማንስ ፡ ሊያበረታ ፡ ማንስ ፡ ሊያግዘኝ
ሰላምም ፡ መፍትሔም ፡ መሆን ፡ የሚቻለው
እውነተኛ ፡ ተስፋ ፡ ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ መድሃኒቴ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ኦሆሆ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም ፡ አሃሃ
እውነተኛ ፡ አዳኝ ፡ ኦሆሆ ፡ ፈዋሽ ፡ የሆንከኝ ፡ አሃሃ
ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ ሌላማ ፡ የለኝም (፪x)
ሃሌሉያ