Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Nefsie Wede Amlakua

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ ነፍሴ ወደ አምላኳ አልበም የናዝሬቱ ኢየሱስ

አዝ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ቶሎ ቶሎ ብዬ ስራዬን ልጨርስ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ሌት ተቀን ልስራና ሥራዬን ልጨርስ

ሲተጉ የሚያገኛቸው ሲመጣ ጌታቸው በመክሊታቸው የሰሩ ምሥጋና አላቸው አገልግሎቱን ያልናቀ በጥቂቱ ታምኖ ብድራቱን ይቀበላል ሥራው ተፈትኖ

አዝ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ቶሎ ቶሎ ብዬ ስራዬን ልጨርስ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ሌት ተቀን ልስራና ሥራዬን ልጨርስ

አደራው ከቶ የማይገዳቸው ቸልተኞች የጌታቸውን መመለስ የረሱ ዝንጉዎች ዕድላቸው ለቅሶ ነውና ዋይታ እንዳይጠብቀኝ መንፈስህ ዘወትር ያንቃኝ ለክብርህ አቁመኝ

አዝ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ቶሎ ቶሎ ብዬ ስራዬን ልጨርስ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ሌት ተቀን ልስራና ሥራዬን ልጨርስ

ጥቂት ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት እንደ ሆነ መች አጣሁት ከቶ የእኔ ሕይወት እንግዲያው ታከተኝ ሳልል ልሩጥ ለጌታዬ የሰነፍ ሰው ሞት እንዳልሞት ልፅና በዓላማዬ

አዝ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ቶሎ ቶሎ ብዬ ስራዬን ልጨርስ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ሌት ተቀን ልስራና ስራዬን ልጨርስ

መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ አበቃሁኝ ኃይማኖትን ጠብቄያለሁ ሩጫውን ጨረስኩኝ እንደ ጳውሎስ ለማለት ተፈፀመ እንደ ኢየሱስ ምሥጋናዬንም እንዳቀርብ ለሠራዊት ንጉሥ

አዝ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ቶሎ ቶሎ ብዬ ስራዬን ልጨርስ ነፍሴ ወደ አምላኳ ሥጋም ወደ አፈሩ ሳይመለስ ሌት ተቀን ልስራና ሥራዬን ልጨርስ