From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ቶሎ ፡ ቶሎ ፡ ብዬ ፡ ስራዬን ፡ ልጨርስ
ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ሌት ፡ ተቀን ፡ ልስራና ፡ ሥራዬን ፡ ልጨርስ
ሲተጉ ፡ የሚያገኛቸው ፡ ሲመጣ ፡ ጌታቸው
በመክሊታቸው ፡ የሰሩ ፡ ምሥጋና ፡ አላቸው
አገልግሎቱን ፡ ያልናቀ ፡ በጥቂቱ ፡ ታምኖ
ብድራቱን ፡ ይቀበላል ፡ ሥራው ፡ ተፈትኖ
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ቶሎ ፡ ቶሎ ፡ ብዬ ፡ ስራዬን ፡ ልጨርስ
ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ሌት ፡ ተቀን ፡ ልስራና ፡ ሥራዬን ፡ ልጨርስ
አደራው ፡ ከቶ ፡ የማይገዳቸው ፡ ቸልተኞች
የጌታቸውን ፡ መመለስ ፡ የረሱ ፡ ዝንጉዎች
ዕድላቸው ፡ ለቅሶ ፡ ነውና ፡ ዋይታ ፡ እንዳይጠብቀኝ
መንፈስህ ፡ ዘወትር ፡ ያንቃኝ ፡ ለክብርህ ፡ አቁመኝ
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ቶሎ ፡ ቶሎ ፡ ብዬ ፡ ስራዬን ፡ ልጨርስ
ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ሌት ፡ ተቀን ፡ ልስራና ፡ ሥራዬን ፡ ልጨርስ
ጥቂት ፡ ታይቶ ፡ ኋላ ፡ እንደሚጠፋ ፡ እንፋሎት
እንደ ፡ ሆነ ፡ መች ፡ አጣሁት ፡ ከቶ ፡ የእኔ ፡ ሕይወት
እንግዲያው ፡ ታከተኝ ፡ ሳልል ፡ ልሩጥ ፡ ለጌታዬ
የሰነፍ ፡ ሞት ፡ እንዳልሞት ፡ ልፅና ፡ በዓላማዬ
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
መልካሙን ፡ ገድል ፡ ተጋድያለሁ ፡ አበቃሁኝ
ኃይማኖትን ፡ ጠብቄያለሁ ፡ ሩጫውን ፡ ጨረስኩኝ
እንደ ፡ ጳውሎስ ፡ ለማለት ፡ ተፈፀመ ፡ እንደ ፡ ኢየሱስ
ምሥጋናዬንም ፡ እንዳቀርብ ፡ ለሠራዊት ፡ ንጉሥ
አዝ፦ ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ቶሎ ፡ ቶሎ ፡ ብዬ ፡ ስራዬን ፡ ልጨርስ
ነፍሴ ፡ ወደ ፡ አምላኳ
ሥጋም ፡ ወደ ፡ አፈሩ ፡ ሳይመለስ
ሌት ፡ ተቀን ፡ ልስራና ፡ ሥራዬን ፡ ልጨርስ
|