Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Nefsie Hoy

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ ነፍሴ ሆይ አልበም የናዝሬቱ ኢየሱስ

ከጥፋት ጉድጓድ ውስጥ ከረግርግ ጭቃ ያወጣኝ እግሬን በድንጋይ ላይ አቁሞ ያፀናኝ በፀጋው ደግፎ በሕይወት ያኖረኝ ከክፉ ፍላጻ በእጁ የከለለኝ

አዝ ነፍሴ ሆይ እግዚአብሔር አምላክ ነውና ስገጂለት መሀሪው ጌታዬ ምሥጋና ይብዛለት በሕይወቴ ሁሉ እኔም ልገዛለት ቸርነቱን ልንገር ምህረቱን ልዘምር ቅኔን ልቀኝለት ኦ ቅኔን ልቀኝለት

ድካምን ህመምን ቁስልን ስብራትን አይቶ ዘመድ ርቆ ሲቆም ኢየሱስ ተጠግቶ በፍቅር አክሞ ሕይወትን ያድሳል ለውለታው ምላሽ ከቶ ምን ይገኛል

አዝ ነፍሴ ሆይ እግዚአብሔር አምላክ ነውና ስገጂለት መሀሪው ጌታዬ ምሥጋና ይብዛለት በሕይወቴ ሁሉ እኔም ልገዛለት ቸርነቱን ልንገር ምህረቱን ልዘምር ቅኔን ልቀኝለት ኦ ቅኔን ልቀኝለት

የጫንቃዬን ሸክም ጌታዬ ደርሶ ጣለልኝ የዕዳዬን ጽሕፈት በሞቱ ሻረልኝ ምህረቱ ድንቅ ነው በእኔ ላይ ያሳየው ከእግሩ ሥር ወድቄ ጌታዬን ላክብረው

አዝ ነፍሴ ሆይ እግዚአብሔር አምላክ ነውና ስገጂለት መሀሪው ጌታዬ ምሥጋና ይብዛለት በሕይወቴ ሁሉ እኔም ልገዛለት ቸርነቱን ልንገር ምህረቱን ልዘምር ቅኔን ልቀኝለት ኦ ቅኔን ልቀኝለት