From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ከአምላካቸው ፡ በቀር ፡ ማንንም ፡ እንዳያመልኩ
ለወርቁ ፡ ምስል ፡ እንዳይሰግዱ ፡ እንዳይንበረከኩ
ሰወነታቸውን ፡ አሳልፈው ፡ የሰጡትን
ወዳጆቹን ፡ ያዳነ ፡ በእርሱ ፡ የታመኑትን [1]
የሲድራቅ ፡ የሚሳቅ ፡ የአብድናጐም ፡ አምላክ
ለዘለዓለም ፡ ይባረክ
እንደ ፡ እርሱ ፡ የሚያድን ፡ ሌላ ፡ አምላክ ፡ የለምና
ከእቶኑ ፡ እሳት ፡ ሊያድናቸው ፡ ችሏልና [1]
ማዳን ፡ የእርሱ ፡ ነውና (፪x)
አዝ፦ ከአምላካቸው ፡ በቀር ፡ ማንንም ፡ እንዳያመልኩ
ለወርቁ ፡ ምስል ፡ እንዳይሰግዱ ፡ እንዳይንበረከኩ
ሰወነታቸውን ፡ አሳልፈው ፡ የሰጡትን
ወዳጆቹን ፡ ያዳነ ፡ በእርሱ ፡ የታመኑትን [1]
የሲድራቅ ፡ የሚሳቅ ፡ የአብድናጐም ፡ አምላክ
ለዘለዓለም ፡ ይባረክ
ጌታ ፡ ተናገረ ፡ እኔም ፡ ይህንን ፡ ብቻ ፡ ሰማሁ
ኃይል ፡ የእግዚአብሔር ፡ መሆኑን ፡ ተገነዘብሁ
እሳቱ ፡ ሲያጠፋ ፡ አየሁ (፪x)
አዝ፦ ከአምላካቸው ፡ በቀር ፡ ማንንም ፡ እንዳያመልኩ
ለወርቁ ፡ ምስል ፡ እንዳይሰግዱ ፡ እንዳይንበረከኩ
ሰወነታቸውን ፡ አሳልፈው ፡ የሰጡትን
ወዳጆቹን ፡ ያዳነ ፡ በእርሱ ፡ የታመኑትን [1]
የሲድራቅ ፡ የሚሳቅ ፡ የአብድናጐም ፡ አምላክ
ለዘለዓለም ፡ ይባረክ
ሰውነታችሁን ፡ ብትሰጡ ፡ ሳትሰስቱ
እግዚአብሔር ፡ ይሰራል ፡ አይፋጅም ፡ ከቶ ፡ እሳቱ
ሥሙን ፡ አስከብሩ ፡ በርቱ (፪x)
አዝ፦ ከአምላካቸው ፡ በቀር ፡ ማንንም ፡ እንዳያመልኩ
ለወርቁ ፡ ምስል ፡ እንዳይሰግዱ ፡ እንዳይንበረከኩ
ሰወነታቸውን ፡ አሳልፈው ፡ የሰጡትን
ወዳጆቹን ፡ ያዳነ ፡ በእርሱ ፡ የታመኑትን [1]
የሲድራቅ ፡ የሚሳቅ ፡ የአብድናጐም ፡ አምላክ
ለዘለዓለም ፡ ይባረክ (፫x)
|