Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Bewnet Asadegen

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ በእውነት አሳድገ አልበም የናዝሬቱ ኢየሱስ

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በክርስትናችን ዕድሜ ቆጥረን በልምምዳችን ኮርተን በትህትና መማሩ ቀረና እድገታችን ቆመ ታበይንና

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

ባስተያየታችን ጠቢባን ነን ትንኝን እናጠራለን ራሳችንን ማንጻት ሳይቻለን የሌላውን ጉድፍ እናያለን

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

ማደጋችንን እዩልን እያልን በከንቱም እየታበይን አንተንም በዚህ እያሳዘንን ሳይታወቀን ስንቶችን ጐዳን

አዝ tesfaye gabiso በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

እንደ ሕጻናት የዋሆች አርገን ንጹህ ልብን መልስልን ዓይናችንን እየገለጥህ አንተው አመላልሰን በብርሃንህ

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በቃል በስርአት ሙታን ሆነን በፍቅር እየታነፅን በእውነት እንደግ ወደ ኢየሱስ እየታበይን እንደምን እንነስ

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር በከንቱ መታበያችን ይቅር በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር