From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በክርስትናችን ፡ ዕድሜ ፡ ቆጥረን
በልምምዳችን ፡ ኮርተን
በትህትና ፡ መማሩ ፡ ቀረና
እድገታችን ፡ ቆመ ፡ ታበይንና
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
ባስተያየታችን ፡ ጠቢባን ፡ ነን
ትንኝን ፡ እናጠራለን
ራሳችንን ፡ ማንጻት ፡ ሳይቻለን
የሌላውን ፡ ጉድፍ ፡ እናያለን
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
ማደጋችንን ፡ እዩልን ፡ እያልን
በከንቱም ፡ እየታበይን
አንተንም ፡ በዚህ ፡ እያሳዘንን
ሳይታወቀን ፡ ስንቶችን ፡ ጐዳን
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
እንደ ፡ ሕጻናት ፡ የዋሆች ፡ አርገን
ንጹህ ፡ ልብን ፡ መልስልን
ዓይናችንን ፡ እየገለጥህ
አንተው ፡ አመላልሰን ፡ በብርሃንህ
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በቃል ፡ በስርአት ፡ ሙታን ፡ ሆነን
በፍቅር ፡ እየታነፅን
በእውነት ፡ እንደግ ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ
እየታበይን ፡ እንደምን ፡ እንነስ
አዝ፦ በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
በከንቱ ፡ መታበያችን ፡ ይቅር
በእውነት ፡ አሳድገን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በፍቅር
|