Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Bewnet Asadegen

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ በእውነት አሳድገ አልበም የናዝሬቱ ኢየሱስ

አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር


በክርስትናችን ዕድሜ ቆጥረን

በልምምዳችን ኮርተን

በትህትና መማሩ ቀረና

እድገታችን ቆመ ታበይንና


አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር


ባስተያየታችን ጠቢባን ነን

ትንኝን እናጠራለን

ራሳችንን ማንጻት ሳይቻለን

የሌላውን ጉድፍ እናያለን


አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር


ማደጋችንን እዩልን እያልን

በከንቱም እየታበይን

አንተንም በዚህ እያሳዘንን

ሳይታወቀን ስንቶችን ጐዳን


አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር


እንደ ሕጻናት የዋሆች አርገን

ንጹህ ልብን መልስልን

ዓይናችንን እየገለጥህ

አንተው አመላልሰን በብርሃንህ


አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር


በቃል በስርአት ሙታን ሆነን

በፍቅር እየታነፅን

በእውነት እንደግ ወደ ኢየሱስ

እየታበይን እንደምን እንነስ


አዝ በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር

በከንቱ መታበያችን ይቅር

በእውነት አሳድገን ጌታ ሆይ በፍቅር