Tesfaye Gabisso/Egziabhier Menfes New/Lamesgeneh Zariem

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ

ርዕስ ላመስግንህ ዛሬም አልበም እግዚአብሔር መንፈስ ነው


ትንፋሼንና መንገዴ ሁሉ በእጅህ ይዘህ

እንደ ዓይንህ ብሌን አርገህ ለእኔ ተጠንቅቀህ

ከሚጐዳኝ ነገር ዘወትር ጋረድክ ሰውረህ

ተመሥገን ከማለት ሌላ ለአንተ ምን ልክፈልህ

አዝ

ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ

ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ

በእውነት አንተ ታማኝ ነህ

ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ


በሀዘን ስመታ ሲከፋኝም አንዳንድ ጊዜ

ከብዶ ሲጫጫነኝ ሲደራረብብኝ ትካዜ

የመፅናናት ጌታ ማን እንደ አንተ ደረሰልኝ

የልቤን ተካፍሎ አይዞህ ሊለኝ ሊያበረታኝ

አዝ

ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ

ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ

በእውነት አንተ ታማኝ ነህ

ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ


ራሴን አውቀው አለሁ እጅግ አስቀያሚ ነበርኩ

ምስኪን አላማ ቢስ በኃጥያት የተቅበዘበዝኩ

ግን እንዲያው ወደኸኝ ሰው ሆኛለሁ በአንተ ብርታት

በቂ ቃል የለኝም ልገልፅ የውለታህን ብዛት


አዝ

ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ

ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ

በእውነት አንተ ታማኝ ነህ

ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ


አህዛብ ባያውቁህም የእኔ ነፍስ ግን ታውቅሃለች

የፍቅር ፊትህን በእየለት ትናፍቃለች

ያለ አባትነትህ መኖር ከቶ አይሆንላትም

መሳይ አጭበርባሪ ሁሉ ከአንተ አይነጥላትም

አዝ


ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ

ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ

በእውነት አንተ ታማኝ ነህ

ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ