Tesfaye Gabisso/Egziabhier Menfes New/Lamesgeneh Zariem

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ ላመስግንህ ዛሬም አልበም እግዚአብሔር መንፈስ ነው

ትንፋሼንና መንገዴ ሁሉ በእጅህ ይዘህ እንደ ዓይንህ ብሌን አርገህ ለእኔ ተጠንቅቀህ ከሚጐዳኝ ነገር ዘወትር ጋረድክ ሰውረህ ተመሥገን ከማለት ሌላ ለአንተ ምን ልክፈልህ

አዝ ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ በእውነት አንተ ታማኝ ነህ ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ

በሀዘን ስመታ ሲከፋኝም አንዳንድ ጊዜ ከብዶ ሲጫጫነኝ ሲደራረብብኝ ትካዜ የመፅናናት ጌታ ማን እንደ አንተ ደረሰልኝ የልቤን ተካፍሎ አይዞህ ሊለኝ ሊያበረታኝ

አዝ ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ በእውነት አንተ ታማኝ ነህ ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ

ራሴን አውቀው አለሁ እጅግ አስቀያሚ ነበርኩ ምስኪን አላማ ቢስ በኃጥያት የተቅበዘበዝኩ ግን እንዲያው ወደኸኝ ሰው ሆኛለሁ በአንተ ብርታት በቂ ቃል የለኝም ልገልፅ የውለታህን ብዛት

አዝ ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ በእውነት አንተ ታማኝ ነህ ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ

አህዛብ ባያውቁህም የእኔ ነፍስ ግን ታውቅሃለች የፍቅር ፊትህን በእየለት ትናፍቃለች ያለ አባትነትህ መኖር ከቶ አይሆንላትም መሳይ አጭበርባሪ ሁሉ ከአንተ አይነጥላትም

አዝ ላመስግንህ ዛሬም የእኔ ጌታ ስለማይነገር ስጦታህ ስላማይቆጠር ውለታህ በእውነት አንተ ታማኝ ነህ ዘላለም ይወደስ ይክበር ታላቅ ሥምህ