Tesfaye Gabisso/Christian Teshagere/Yeseralegnen Denq

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ የሰራልኝን ድንቅ አልበም ክርስቲያን ተሻገረ

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በእለት እርምጃዬ እግሬ ኢየሱስ ቀድሞ ምህረቱን አብዝቶ ተዓምራቱን ደግሞ አሳየኝ አምላኬ የከበረ ነገር እንደዚህ ሊመራኝ ወደ ፃድቃን አገር (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በቀኝ በግራዬ አድፍጦ አድብቶ መልካም መሰል አጥፊ ወጥመዱን ዘርግቶ ጌታ ግን ሲያድነኝ በጦር ተደራጅቶ ዲያብሎስ ሊያጠቃኝ ነበር ተሰናድቶ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

እርሱ ቅጥር ሲቀጥር በእምላኬ እየዘለልኩ ወጥመድ ሲዘረጋ እኔም እያመለጥኩ በእኔ ብርታት ሳይሆን በጌታ እየታመንኩ ሩጫ ቀጥላለሁ ሁሉን እያሸነፍኩ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በዘለዓለም መድህን ከጥልቁ ወጥቼ ከአባት ከእናት ዘመድ የሚበልጥ አግኝቼ በአህዛብ መሃከል ለርሱ ዘምራለሁ የከበረ ሥሙን አመሰግናለሁ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪×)