Tesfaye Gabisso/Christian Teshagere/Yeseralegnen Denq

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ የሰራልኝን ድንቅ አልበም ክርስቲያን ተሻገረ

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በእለት እርምጃዬ እግሬ ኢየሱስ ቀድሞ ምህረቱን አብዝቶ ተዓምራቱን ደግሞ አሳየኝ አምላኬ የከበረ ነገር እንደዚህ ሊመራኝ ወደ ፃድቃን አገር (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በቀኝ በግራዬ አድፍጦ አድብቶ መልካም መሰል አጥፊ ወጥመዱን ዘርግቶ ጌታ ግን ሲያድነኝ በጦር ተደራጅቶ ዲያብሎስ ሊያጠቃኝ ነበር ተሰናድቶ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

እርሱ ቅጥር ሲቀጥር በእምላኬ እየዘለልኩ ወጥመድ ሲዘረጋ እኔም እያመለጥኩ በእኔ ብርታት ሳይሆን በጌታ እየታመንኩ ሩጫ ቀጥላለሁ ሁሉን እያሸነፍኩ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪)

በዘለዓለም መድህን ከጥልቁ ወጥቼ ከአባት ከእናት ዘመድ የሚበልጥ አግኝቼ በአህዛብ መሃከል ለርሱ ዘምራለሁ የከበረ ሥሙን አመሰግናለሁ (፪x)

አዝ የሰራልኝን ድንቅ ታሪኩን ላውጋችሁ ሰዎች እስኪ ስሙ ትምህርት ይሁናችሁ በጌታ ይታመን ይጽናና ልባችሁ (፪×)