From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ሰማይን ፡ የሰራ ፡ የምድርም ፡ ፈጣሪ
በዘለዓለም ፡ ዙፋን ፡ ለዘለዓለም ፡ ኗሪ
ገናናነትህን ፡ ሰማያት ፡ ያውቃሉ
ምድርና ፡ ሞላዋም ፡ ይመሰክራሉ
አዝ፦ የኃያላን ፡ ሁሉ ፡ ኃያል ፡ ነህ
የነገሥታት ፡ ሁሉ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ
የጌቶችም ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ ነህ
ባለ ፡ ታላቅ ፡ ግርማ ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነህ
በነገስህ ፡ ጊዜ ፡ ክብርህን ፡ ስትለብስ
ለተጠቃው ፡ ህዝብህ ፡ ፊትህን ፡ ስትመልስ
ድንቅ ፡ አድራጐትህን ፡ በምድር ፡ ስታደርግ
በጽድቅህ ፡ ስትፈርድ ፡ አመጻን ፡ ስትጠርግ
አዝ፦ የኃያላን ፡ ሁሉ ፡ ኃያል ፡ ነህ
የነገሥታት ፡ ሁሉ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ
የጌቶችም ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ ነህ
ባለ ፡ ታላቅ ፡ ግርማ ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነህ
ቃልህን ፡ ስትሰጥ ፡ በሲና ፡ ተራራ
በልጆችህ ፡ ሰፈር ፡ በበረሃው ፡ ስፍራ
በክብር ፡ እሳትህ ፡ ተራራውን ፡ አጤስከው
በመረጥካቸው ፡ ፊት ፡ ክብርህን ፡ ገለጽከው
አዝ፦ የኃያላን ፡ ሁሉ ፡ ኃያል ፡ ነህ
የነገሥታት ፡ ሁሉ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ
የጌቶችም ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ ነህ
ባለ ፡ ታላቅ ፡ ግርማ ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነህ
የተዳፈሩህን ፡ የተነሱብህን
ልክህን ፡ ሳያውቁ ፡ የታጠቁብህን
እየቀጣሃቸው ፡ ተረቶች ፡ ሆነዋል
ተፈርተህ ፡ ተከብረህ ፡ አንተ ፡ ግን ፡ ኖረሃል
አዝ፦ የኃያላን ፡ ሁሉ ፡ ኃያል ፡ ነህ
የነገሥታት ፡ ሁሉ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ
የጌቶችም ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ ነህ
ባለ ፡ ታላቅ ፡ ግርማ ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነህ (፪x)
|