Tesfaye Gabisso/Awon Yehonal/Serah Yamesegenehal

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ ሥራህ ያመሰግንሃል

ሥራህ ያመሰግንሃል ቅዱሳን ያከብሩሃል ጌትነትህም ገብቷቸው ተንበርክኳል ጉልበታቸው

አዝ ሃሌሉያ ተመስገን ጌታ ተመስገን ተመስገን (፫x) ኢየሱስ ተመስገን

እውነትህን ጠብቀሃል ለተበደሉት ፈርደሃል የተጠቃውን ታድገሃል በማዳንህ ከፍ ብለሃል

አዝ ሃሌሉያ ተመስገን ጌታ ተመስገን ተመስገን (፫x) ኢየሱስ ተመስገን

ደሃ አደጉን ተቀብለህ ለተራበ ምግብን ሰጥተህ ምጻተኛ አስጠግተሃል ግዞተኛውን ፈተሃል

አዝ ሃሌሉያ ተመስገን ጌታ ተመስገን ተመስገን (፫x) ኢየሱስ ተመስገን

የተቀደሰ ሥምህን በዜማ ቅኔ ላመስግን በአንተ ሆኖልኝ የመዳን ቀን ስለወጣሁ ከሰቀቀን

አዝ ሃሌሉያ ተመስገን ጌታ ተመስገን ተመስገን (፫x) ኢየሱስ ተመስገን