ማሰሮው ፡ ሲሰበር (Maserow Siseber) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 3:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

ማሰሮው ፡ ሲሰበር ፡ ድብቁ ፡ ብርሃን ፡ ይወጣል
ስንዴው ፡ ሲበሰብስ ፡ ቡቃያው ፡ ብዙ ፡ ያፈራል
ጌታዬ ፡ አምላኬ ፡ የተሰበረ ፡ ልብ ፡ ያሻኛል

ድምፅህን ፡ እንድሰማ ፡ የተግሳጽ ፡ ይሁን ፡ ወይም ፡ የምክር
በድንግዝግዝ ፡ ጊዜ ፡ ወድቄ ፡ እንዳልሰበር
ጌታዬ ፡ አምላኬ ፡ የተከፈተ ፡ ጆሮ ፡ ያሻኛል

አንተን ፡ ለመመልከት ፡ ሁልጊዜ ፡ በፊቴ ፡ ስትሄድ
ወደ ፡ ቀጠሮአችን ፡ ቦታ ፡ በብርሃንህ ፡ እንድራመድ
ጌታዬ ፡ አምላኬ ፡ ጤንነት ፡ ያለው ፡ ዓይን ፡ ያሻኛል

ሰላምን ፡ ለማውራት ፡ የምሥራች ፡ ይዤ ፡ እንድሮጥ
ፅድቅን ፡ ለተጠሙ ፡ ምንጩን ፡ እነሆ ፡ ለማለት
ጌታዬ ፡ አምላኬ ፡ የሚራመዱ ፡ እግሮች ፡ ያሹኛል