Tesfaye Gabisso/Abietu Mebareken Barken/Abietu Mebareken Barken

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ አቤቱ መባረክን ባርከን አልበም አቤቱ መባረክን ባርከን

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ

ያቤጽንም ሰምተሃል እንደዚህ ሲለምንህ ነፍሱን ባርከህለታል አገሩንም አስፍተህ

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ

በልጅህ ስቃይና በጣር የተወለድን እኛም ፍሬዎችህ ነን አስባስበህ ጠብቀን

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህየእኛ ተስፋ

ከፊትህ አትጣለን እንማጸንሃለን በሞገስህ አስበን በምህረትህ ጐብኘን

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ

ሰማያቱም ይከፈቱ መንፈስህ ይፍሰስልን ሕይወታችን ትረስርስ ነፍሳችን ትጥገብልን

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ

ብቻችንን አንቅር አብዛን እየባረክህ አበልጽገን በፀጋህ ታደገን በቃልህ

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ

እግዚአብሔርን በማወቅ ምድር እስክትሞላ ምልጃችን ይቀጥላል ጉልበታችን ሳይላላ

አዝ አቤቱ መባረክን ባርከን አገራችንን አስፋ እጅህም በእኛ ላይ ትሁን አንተ ነህ የእኛ ተስፋ