ማዕረጌ ፡ ነህ (Maeregie Neh) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 4.jpg


(4)

የበላይ ፡ ነህ ፡ ጌታ
(Yebelay Neh Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 6:39
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

አዝ:- ማን ፡ እንዳንተ ፡ ይሆናል
ማንስ ፡ ልብን ፡ ይረዳል
ለእኔስ ፡ ሁሉን ፡ ሆንክልኝ
ጌታ ፡ በአንተ ፡ አማረብኝ

ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ጋሻዬ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ/ውበቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

ያማረብኝ ፡ በአንተ ፡ አሃሃሃ
ወግ ፡ ያየሁት ፡ በአንተ ፡ አሃሃሃ
ሚስጥሩ ፡ ያልገባው ፡ ጥግ ፡ ሆኖ ፡ ቢተቸኝ
ያሰኘውን ፡ ይበል ፡ ኧረ ፡ እኔን ፡ አይረብሸኝ
ከርግሮህ ፡ ስር ፡ ወድቂ ፡ አሃሃሃ
ፈቅጄ ፡ አመልካለሁ ፡ አሃሃሃ
መሸ ፡ ነጋ ፡ አልልም ፡ ኑሮዬ ፡ አምልኮ ፡ ነው

አዝ:- ማን ፡ እንዳንተ ፡ ይሆናል
ማንስ ፡ ልብን ፡ ይረዳል
ለእኔስ ፡ ሁሉን ፡ ሆንክልኝ
ጌታ ፡ በአንተ ፡ አማረብኝ

ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ጋሻዬ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ/ውበቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

ያ ፡ ውድ ፡ መዓዛው ፡ ዙፋንህን ፡ ይክበበው
የከበረውን ፡ ሽቶ ፡ ከእግርህ ፡ ስር ፡ ልስበረው
ክብሬን ፡ እየጣልኩ ፡ ክብር ፡ እሰጥሃለሁ
በሁለንተናዬ ፡ ላመልክህ ፡ ቆርጫለሁ

አመልካለሁ ፡ ክብሬን ፡ እየጣለኩ
አመልካለሁ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ
አመልካለሁ ፡ የመኖሬ ፡ ትርጉም
አመልካለሁ ፡ ሚስጥሩ ፡ በአንተ ፡ ነው (፪x)

ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ጋሻዬ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ውበቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

አዝ:- ማን ፡ እንዳንተ ፡ ይሆናል
ማንስ ፡ ልብን ፡ ይረዳል
ለእኔስ ፡ ሁሉን ፡ ሆንክልኝ
ጌታ ፡ በአንተ ፡ አማረብኝ

ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ጋሻዬ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም
ትምክቴ/ውበቴ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም (፪x)