Tesfaye Chala/Lebarkew Gietayien Lebarkew/Keber Lehonen Gieta

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

አዝ

ክበር የሆነን ጌታ ሞገስ የሆነን ጌታ ብቃት የሆነን ጌታ በጉድለታችን ፈንታ ክንዱን በዘመናችን በዓይናችን አይተነዋል መልካም እረኛ ኢየሱስ እስከዛሬ ረድቶናል

በዘመን በአመታት መሃል የሚገዳደረው የታል ብቻውን ድንቅ እየሰራ የሚኖር እንደተፈራ ለእኛም ይሄው ሞገስ ሆነን ባሕሩን ከፍሎ አሻገረን ችግራችንን እረሳነው በኢየሱስ ስንቱን አለፍን

አዝ ክበር የሆነን ጌታ...

ስንቱን ተሻገርን አለፍን በምሥጋና ሆ እያልን ስንቱስ ከእግራችን ወደቀ በኢየሱስ እየደቀቀ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ሲተካ ፍሬያችን አብቦ ፈካ የረገጥነውን ወረስን እለት እለት አማረብን

አዝ ክበር የሆነን ጌታ...

በምድረ በዳ በረሃ የሚያረካ ውኃ ሆነን አልሰለቸን የእኛ ጌታ እንደቃሉ ተለመነን በመከራ ቀን ሰቀቀን ተማምነን ስሙን ስንጠራ ደረሰልን በሰአቱ ኢየሱስ ጌታ የሚያኮራ

አዝ ክበር የሆነን ጌታ...

ሸንጐ በእኛ ላይ ሲማከር ዲያብሎስ ሊያጠፋን ሲጥር ማነው ደርሶ የታደገን በመከራ መርከብ ሆነን ታሪክ ይናገር ብዙ ነው ብዙ ነው እኛስ ያለፍነው ከእግራችን ስር ወድቆ ጠላት ጭንቅላቱን እረገጥነው

አዝ ክበር የሆነን ጌታ...