Tesfaye Chala/Lebarkew Gietayien Lebarkew/Keber Lehonen Gieta

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

አዝ

ክበር የሆነን ጌታ
ሞገስ የሆነን ጌታ
ብቃት የሆነን ጌታ
በጉድለታችን ፈንታ
ክንዱን በዘመናችን በዓይናችን አይተነዋል
መልካም እረኛ ኢየሱስ እስከዛሬ ረድቶናል

በዘመን በአመታት መሃል
የሚገዳደረው የታል


ብቻውን ድንቅ እየሰራ
የሚኖር እንደተፈራ
ለእኛም ይሄው ሞገስ ሆነን
ባሕሩን ከፍሎ አሻገረን
ችግራችንን እረሳነው በኢየሱስ ስንቱን አለፍን


አዝ ክበር የሆነን ጌታ...


ስንቱን ተሻገርን አለፍን
በምሥጋና ሆ እያልን
ስንቱስ ከእግራችን ወደቀ
በኢየሱስ እየደቀቀ
ዘመን ሲያልፍ ዘመን ሲተካ ፍሬያችን አብቦ ፈካ
የረገጥነውን ወረስን
እለት እለት አማረብን


አዝ ክበር የሆነን ጌታ...


በምድረ በዳ በረሃ የሚያረካ ውኃ ሆነን
አልሰለቸን የእኛ ጌታ እንደቃሉ ተለመነን
በመከራ ቀን ሰቀቀን ተማምነን ስሙን ስንጠራ
ደረሰልን በሰአቱ ኢየሱስ ጌታ የሚያኮራ
አዝ ክበር የሆነን ጌታ...


ሸንጐ በእኛ ላይ ሲማከር
ዲያብሎስ ሊያጠፋን ሲጥር
ማነው ደርሶ የታደገን
በመከራ መርከብ ሆነን
ታሪክ ይናገር ብዙ ነው
ብዙ ነው እኛስ ያለፍነው
ከእግራችን ስር ወድቆ ጠላት ጭንቅላቱን እረገጥነው


አዝ ክበር የሆነን ጌታ...