ምህረትህን ፡ አይቻለሁ (Meheretehen Aychalehu) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Lyrics.jpg


(1)

ባማረ ፡ ቅኔ
(Bamare Qenie)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 6:33
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

አዝውዴ (፫x) ፡ ኢየሱስ (፫x)
ምህረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ አወራለሁ
ምሕረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ ዘምራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ አወራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ ዘምራለሁ (፪x)

አስራ ፡ ሁለት ፡ ዓመት ፡ ደም ፡ እየፈሰሰኝ
ተነጥዬ ፡ መኖር ፡ ሰው ፡ እንኳን ፡ እራቀኝ
ከእንግዲህስ ፡ ወዲያ ፡ ተስፋዬ ፡ ምንድን ፡ ነው
ዕድሜዬ ፡ በሙሉ ፡ በለቅሶ ፡ ሊያልቅ ፡ ነው
ብዬ ፡ ደምድሜ ፡ ሃሳቤን ፡ ስጠብቀው ፡ ፍጻሚዬን
ድንገት: ብርሃን: ወጣልኝ: አዳኜ ፡ ኢየሱስ ፡ መጣልኝ

አዝውዴ (፫x) ፡ ኢየሱስ (፫x)
ምህረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ አወራለሁ
ምሕረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ ዘምራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ አወራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ ዘምራለሁ

ግርግሩ ፡ በዝቶ ፡ የሚጋፋው ፡ ሰው
አዳኜ ፡ ኢየሱስን ፡ እንዴት ፡ ላግኘው
ተስፋ ፡ ባለመቁረጥ ፡ እየተንፉቀኩኝ
እጄን ፡ ሰደድኩና ፡ ቀሚሱን ፡ ነካሁኝ
ነካ ፡ ባደርገው ፡ ነካኝ ፡ ኃይልም ፡ ወጣና ፡ ዳንኩኝ
ታዲያ ፡ ምን ፡ ልበል ፡ ይህን ፡ ጌታ ፡ አመስግኑልኝ ፡ በልልታ

አዝውዴ (፫x) ፡ ኢየሱስ (፫x)
ምህረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ አወራለሁ
ምሕረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ ዘምራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ አወራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ ዘምራለሁ

ዘመናት ፡ አለፉ ፡ ሆኜ ፡ በጭንቀት
ለደሜ ፡ ማድረቂያ ፡ ጠፍቶ ፡ መድሐኒት
ማንም ፡ ማይጠጋኝ ፡ እርኩስ: ናት: ተብዬ
አሁንስ ፡ መረረኝ ፡ ገላግለኝ ፡ ጌታዬ
ብዬ ፡ ሞቴንም ፡ ስናፍቅ ፡ በሽታዬ: አርጎኝ: ድቅቅ
መሲሁ ፡ መጣልኝና ፡ አቆመኝ ፡ ፈወሰኝና

አዝውዴ (፫x) ፡ ኢየሱስ (፫x)
ምህረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ አወራለሁ
ምሕረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ ዘምራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ አወራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ ዘምራለሁ

ትድናለች ፡ ብሎ ፡ ኧረ ፡ ማን ፡ ገመተኝ
ሁሉም ፡ በሩቅ ፡ ሲሸሽ፡ ጀርባውን ፡ ሲሰጠኝ
አስታማሚ ፡ አጥቼ ፡ የምደግፈኝ
ኢየሱስ ፡ ሲጐበኘኝ ፡ በዛ ፡ ሚያጅበኝ
የሸሹኝ ፡ ሁሉ ፡ አቀፉኝ፡ የናቁኝ ፡ ሁሉ ፡ አከበሩኝ
መሸማቀቄም ፡ ቀረልኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ይመስገንልኝ

አዝውዴ (፫x) ፡ ኢየሱስ (፫x)
ምህረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ አወራለሁ
ምሕረትህን ፡ አይቻለሁ ፡ ዘምራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ አወራለሁ
ማዳንህን ፡ ቀምሻለሁ ፡ ዘምራለሁ