Teodros Tadesse/Wa/Adegedegalew
ደሞ ፡ ልቀኝ ፡ ነዉ ፡ ዘመን ፡ መጣልኝ ፡ አሆ ፡ ዘመን ፡ መጣልኝ ገብቼ ፡ ለማጠን ፡ ዕጣ ፡ ወጣልኝ ፡ አሆ ፡ ተራዉ ፡ ደረሰኝ መታደል ፡ ነዉ ፡ መታደል ፡ ይሄን ጌታ ፡ ማገልገል መታደል ፡ ነዉ ፡ መታደል ፡ ይሄን ፡ ጌታ ፡ ማገልገል
አዝ ፡ - አደገድጋለዉ ፡ በፊቱ ፡ ልብሰ ፡ ተክኖዬን ፡ ለብሼ
- የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ ካህን ፡ ነኝና ፡ ገባዉ ፡ ላመልከዉ ፡ መቅረዜን ፡ ለኩሼ
- ተደርጎልኛል ፡ ተደርጎልኛል ፡ ዝምታ ፡ በእኔ ፡ መች ፡ ያምርብኛል
- ተፈቅዶልኛል ፡ ተፈቅዶልኛል ፡ የፈሰሰዉ ፡ ደም ፡ እለፍ ፡ ብሎኛል
እንደ ፡ አቤል ፡ መሥወእት ፡ ከተቀበለልኝ ፡ የእኔንም ፡ ዝማሬ እርሱን ፡ ደስ ፡ ካለዉ ፡ ዘመኔ ፡ ይጠቅለል ፡ ዘምሬ ፡ ዘምሬ መዝሙር ፡ አላቆምም ፡ እስትንፋሴ ፡ እስካለች ፡ በዚች ፡ ምድር ፡ ላይ ሌላ ፡ ምን ፡ ስራ ፡ አለኝ ፡ የተፈጠርኩትስ ፡ ለዚማ ፡ አይደል ፡ ሆይ
አሆ ፡ ያርግልኝ ፡ አሆ ፡ አምልኮዬ ፡ አሆ ፡ ያለኝ ፡ ይኽዉ ፡ አሆ ፡ ይኽዉ ፡ ስጦታዬ አሆ ፡ ያርግልኝ ፡ አሆ ፡ አምልኮዬ ፡ አሆ ፡ ያለኝ ፡ ይኽዉ ፡ አሆ ፡ ይኽዉ ፡ ዕልልታዬ ይገባዋል ፡ እለዋለሁ ፡ በሙሉ ፡ ክብሩ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ ይገባዋል ፡ እለዋለሁ ፡ በሞገሱ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ
ቃሉ ፡ ነግሮኛል ፡ ተከፍቷል ፡ ብሎኛል ፡ ቅዱስተ ፡ ቅዱሳን ፡ መግባት ፡ ሆኖልኛል ቃሉ ፡ ነግሮኛል ፡ ተከፍቷል ፡ ብሎኛል ፡ ቅዱስተ ፡ ቅዱሳን ፡ መግባት ፡ ሆኖልኛል
ደሞ ፡ ልቀኝ ፡ ነዉ ፡ ዘመን ፡ መጣልኝ ፡ አሆ ፡ ዘመን ፡ መጣልኝ ገብቼ ፡ ለማጠን ፡ ዕጣ ፡ ወጣልኝ ፡ አሆ ፡ ተራዉ ፡ ደረሰኝ መታደል ፡ ነዉ ፡ መታደል ፡ ይሄን ጌታ ፡ ማገልገል መታደል ፡ ነዉ ፡ መታደል ፡ ይሄን ፡ ጌታ ፡ ማገልገል
አዝ ፡ - አደገድጋለዉ ፡ በፊቱ ፡ ልብሰ ፡ ተክኖዬን ፡ ለብሼ የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ ካህን ነኝና ፡ ገባዉ ፡ ላመልከዉ ፡ መቅረዜን ፡ ለኩሼ ተደርጎልኛል ፡ ተደርጎልኛል ፡ ዝምታ ፡ በእኔ ፡ መች ፡ ያምርብኛል ተፈቅዶልኛል ፡ ተፈቅዶልኛል ፡ የፈሰሰዉ ፡ ደም ፡ እለፍ ፡ ብሎኛል
ከላይ ፡ ከዓርያም ፡ በዙፋኑ ፡ ላለዉ ፡ በሱር ፡ ፀባኦቱ ሲዘምሩ ፡ ሰማዉ ፡ ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ሲሉ ፡ ዜማቸዉ ፡ ዉበቱ ሽታዉ ፡ ያዉደኛል ፡ የአምልኮ ፡ መዓዛ ፡ ይሄ ፡ ህልዉና ነፍስ ፡ አይቀርልኝም ፡ ወርዶ ፡ ሲሸፍ ፡ ነኝ ፡ የክብሩ ፡ ደመና
አሆ ፡ ያርግልኝ ፡ አሆ ፡ አምልኮዬ አሆ ፡ ያለኝ ፡ ይኽዉ ፡ አሆ ፡ ይኽዉ ፡ ስጦታዬ አሆ ፡ ያርግልኝ ፡ አሆ ፡ አምልኮዬ አሆ ፡ ያለኝ ፡ ይኽዉ ፡ አሆ ፡ ይኽዉ ፡ ዕልልታዬ
ይገባዋል ፡ እለዋለሁ ፡ በሙሉ ፡ ክብሩ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ ይገባዋል ፡ እለዋለሁ ፡ በሙሉ ፡ በሞገሱ ፡ ፊቱን ፡ እያየሁ
ቃሉ ፡ ነግሮኛል ፡ ተከፍቷል ፡ ብሎኛል ፡ ቅዱስተ ፡ ቅዱሳን ፡ መግባት ፡ ሆኖልኛል ቃሉን ፡ ነግሮኛል ፡ ተከፍቷል ፡ ብሎኛል ፡ ቅዱስተ ፡ ቅዱሳን ፡ መግባት ፡ ሆኖልኛል }}