በእውነት ፡ ለሚወዱህ (Bewnet Lemiweduh) - ተመስገን ፡ ማርቆስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተመስገን ፡ ማርቆስ
(Temesgen Markos)

Temesgen Markos 1.png


(1)

ፋሬስ
(Fares)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2003)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተመስገን ፡ ማርቆስ ፡ አልበሞች
(Albums by Temesgen Markos)

አዝ፦ በእውነት ፡ ለሚወዱህ ፡ እንደሃሳብህ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ሁሉ (፰x)

መገፋት ፡ መሰደዴ ፡ ወደ ፡ ግብጽም ፡ መውረዴ
ወዶኝ ፡ ነው ፡ ያደረገው ፡ አላማ ፡ በእኔ ፡ ስላለው
ወጣሁ ፡ ቀኑ ፡ ደርሶ ፡ የበላይ ፡ አደረገኝ
ተሾምኩኝ ፡ ተመረጥኩኝ ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ሆነልኝ (፪x)
ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ሆነልኝ (፬x)

አዝ፦ በእውነት ፡ ለሚወዱህ ፡ እንደሃሳብህ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ሁሉ (፬x)

ሃዘን ፡ ሆነ ፡ መቸገሬ ፡ ኋላ ፡ ግን ፡ ሆነ ፡ ለክብሬ
አለፍኩት ፡ እንደዋዛ ፡ መከራዬ ፡ ረግፎ ፡ እንደጤዛ
ኑሮዬን ፡ እንዲህ ፡ አጣፍጦ ፡ ዘመርኩኝ ፡ ሁሉ ፡ ተረስቶ
ሆነልኝ ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ጌታ ፡ ነገሬን ፡ ውብ ፡ አድርጐ (፪x)
ጌታ ፡ ነገሬን ፡ ውብ ፡ አድርጐ (፬x)

አዝ፦ በእውነት ፡ ለሚወዱህ ፡ እንደሃሳብህ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ሁሉ (፬x)

አይበቃም ፡ እዘምራለሁ ፡ ለአምላኬ ፡ እኔ ፡ እቀኛለሁ
አምሮልኝ ፡ ሁሉ ፡ ውብ ፡ ሆኗል ፡ መከራዬ ፡ ድልድይ ፡ ሆኖኛል
ተሻገርኩ ፡ ሁሉን ፡ አልፌ ፡ አለሁኝ ፡ ከሞት ፡ ተርፌ
አይቶልኝ ፡ እዚህ ፡ አድርሶኛል ፡ አክብሮ ፡ ያዘምረኛል (፪x)
አክብሮ ፡ ያዘምረኛል (፬x)

አዝ፦ በእውነት ፡ ለሚወዱህ ፡ እንደሃሳብህ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ሁሉ (፰x)