Temesgen Abera/Singles/Egrehen Letebeh

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የምትናፈቅ ፡ የክረምቷ ፡ ፀሀይ ሙቀቷን ፡ ፍጥረት ፡ ፈልጎ ፡ ሰማይ ፡ ሰማይ ፡ ሲያይ ብትወጣ ፡ ጭጋጉን ፡ አልፋ ብትቀር ፡ በደመና ፡ ተውጣ ፡ ህይወት ፡ አይቀርም ፡ ዑደቱ በቀዝቃዛው ፡ አየር ፡ ዙረቱ አማራጭ ፡ የሌላት ፡ ነፍሴ ፡ ግን ፡ ሺ ፡ ፀሀይ ፡ ቢወጣ ፡ አይሞቃትም ውበቷ ፡ ክብሯ ፡ አንተ ፡ ነህ ከእልፍ ፡ አእላፋት ፡ መካከል ፡ አንድም ክብር የለም

ዋላ ፡ ወደ ፡ ውሀ ፡ ምንጭ ፡ እንደምትናፍቅ ነፍሴ ፡ ገሰገሰች ፡ አንተን ፡ አንተን ፡ አለች

አትሂድ ፡ ከደጄ ፡ ወዳጄ ፡ ቤቴ ፡ ግባ እግርህን ፡ ልጠብህ ፡ እባክህ ፡ አረፍ ፡ በልና እንግዶችን ፡ ልሸኝ ፡ ገፍተው ፡ ከልፍኝ ፡ ያራቁህን ደምቀህ ፡ እንዳትታይ ፡ በምክር ፡ የሚያቀሉህን

አሀሀ ፡ ደጆች ፡ ይከፈቱ አሀሀ ፡ ፡ የክብር ፡ ንጉስ ፡ ይግባ አሀሀ ፡ ይህ ፡ የክብር ፡ ንጉስ ፡ ማነው አሀሀ ፡ የጭፍሮች ፡ አምላክ ፡ እ/ር ፡ ነው.....አሃሃ

ያላንተ ፡ አይሆንልኝም ፡ ወዳጄ አረ ፡ እንዴት ፡ ይሆንልኛል ፡ አንተን ፡ ገፍቼ ኑርና ፡ ልኑር ፡ በህይወት ስትኖር ፡ ነው ፡ ኖርኩኝ ፡ ማለት ከኔ ፡ መኖር ፡ ይልቅ ፡ ይሻላል ሰው ፡ ብቻውን ፡ ምን ፡ ይፈይዳል ያለ ፡ እኔ ፡ መኖር ፡ የምትችል ከአንተ ፡ ውጭ ፡ መኖር ፡ የማልችል.....አሃአሃአሃ ስለሆንኩ ፡ አትውሰድብኝ እሳቱን ፡ ከመቅረዙ ፡ ላይ ዘውትር ፡ ይንደድልኝ

ዋላ ፡ ወደ ፡ ውሀ ፡ ምንጭ ፡ እንደምትናፍቅ ነፍሴ ፡ ገሰገሰች ፡ አንተን ፡ አንተን ፡ አለች

ሰው ፡ እንደሚናኖረው ፡ ለመኖር ፡ ተመሳስዬ አልቻልኩም ፡ በእንጀራ ፡ ለመዝለቅ ፡ ነፍሴን ፡ አታልዬ የትም ፡ እንደማልደርስ ፡ ገብቶኛል ፡ በእኔ ፡ እሩጫ እግሬን ፡ በፈቃድህ ፡ እሰረው ፡ እስከመጨረሻ

አሀሀ ፡ ደጆች ፡ ይከፈቱ አሀሀ ፡ ፡ የክብር ፡ ንጉስ ፡ ይግባ አሀሀ ፡ ይህ ፡ የክብር ፡ ንጉስ ፡ ማነው አሀሀ ፡ የጭፍሮች ፡ አምላክ ፡ እ/ር ፡ ነው.....አሃሃ