From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አንደበቴ ፡ ከምስጋና ፡ በቀር ፡ ሌላ ፡ አያውቅም
ይዘምራል ፡ ላንተ ፡ ክብር ፡ ሰለቸኝ ፡ አይልም
ደግነትህ ፡ በሕይወቴ ፡ እጅግ ፡ ስለበዛ
አሳጣኸኝ ፡ ከቶ ፡ ምለው ፡ ከምሥጋና ፡ ሌላ (፪x)
አዝ፦ ምክንያቴ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አጥንቶቼም ፡ በርቱ ፡ ለአምላኬ ፡ ተገዙ
ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ አክብሪው ፡ ከሞት ፡ ያዳነሽን
ዝም ፡ አትበይ ፡ ተነሽ ፡ አመስግኝ ፡ ጌታሽን (፪x)
ከቶ ፡ አልሻም ፡ በዘመኔ ፡ ካንተ ፡ ሌላ ፡ ለኔ
ቆርጫለሁ ፡ ላልለይህ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
ብቻ ፡ አንተ ፡ ክበር ፡ እንጂ ፡ ይሁን ፡ ደስ ፡ እንዳለህ
አልሰለችም ፡ ሁልጊዜ ፡ ጌታዬ ፡ ባከብርህ (፪x)
አዝ፦ ምክንያቴ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አጥንቶቼም ፡ በርቱ ፡ ለአምላኬ ፡ ተገዙ
ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ አክብሪው ፡ ከሞት ፡ ያዳነሽን
ዝም ፡ አትበይ ፡ ተነሽ ፡ አመስግኝ ፡ ጌታሽን (፪x)
ልማድህ ፡ ነው ፡ ከፍ ፡ ማድረግ ፡ ከብረህ ፡ የምታከብር
ትቢያ ፡ አራግፈህ ፡ መሸላለም ፡ ማብቃት ፡ ለቁም ፡ ነገር
ስንቱ ፡ አረፈ ፡ እፎይ ፡ አለ ፡ ወዳንተ ፡ ሲጠጋ
አመለጠ ፡ ባንተ ፡ ጉልበት ፡ ከጠላት ፡ መንጋጋ (፪x)
አዝ፦ ምክንያቴ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ብዙ
አጥንቶቼም ፡ በርቱ ፡ ለአምላኬ ፡ ተገዙ
ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ አክብሪው ፡ ከሞት ፡ ያዳነሽን
ዝም ፡ አትበይ ፡ ተነሽ ፡ አመስግኝ ፡ ጌታሽን (፪x)
በምስጋና ፡ ላይ ፡ ምስጋና ፡ ገና ፡ አበዛለሁ
ተባረክ ፡ ብዬ ፡ ሁልጊዜ ፡ መቼ ፡ እጠግባለሁ (፪x)
በዝማሬ ፡ ላይ ፡ ዝማሬ ፡ ገና ፡ አበዛለሁ
ተባረክ ፡ ብዬ ፡ ሁልጊዜ ፡ መቼ ፡ እጠግባለሁ (፪x)
|