From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ልሰዋ ፡ የምሥጋናን ፡ መስዋዕት
ሆነኸኝ ፡ አይቻለሁ ፡ አባት
ላክብርህ ፡ እኔ ፡ ደጋግሜ
ከፍ ፡ በል ፡ ላዚም ፡ ፊትህ ፡ ቆሜ (፪x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
ተራራው ፡ ከፊቴ ፡ እንደሰም ፡ ቀለጠ ፡ (ምሥጋናዬን)
ቃልህም ፡ ሲመጣ ፡ ጫካው ፡ ተገለጠ ፡ (ምሥጋናዬን)
እግሮቼም ፡ ጸኑልኝ ፡ እንደዋላ ፡ እግር ፡ (ምሥጋናዬን)
ረዳት ፡ ሆነኸኛል ፡ አምላኬ ፡ ክበር ፡ (ምሥጋናዬን)
አዝ፦ ልሰዋ ፡ የምሥጋናን ፡ መስዋዕት
ሆነኸኝ ፡ አይቻለሁ ፡ አባት
ላክብርህ ፡ እኔ ፡ ደጋግሜ
ከፍ ፡ በል ፡ ላዚም ፡ ፊትህ ፡ ቆሜ (፪x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
ምህረትህ ፡ ከሕይወት ፡ በእርግጥም ፡ ይበልጣል ፡ (ምሥጋናዬን)
ደጅ ፡ ጥናት ፡ የለም ፡ በፍጥነት ፡ ያነሳል ፡ (ምሥጋናዬን)
ድንጋይ ፡ ተደርድሮ ፡ ሞት ፡ ሲጠብቃት ፡ (ምሥጋናዬን)
አፍረቷን ፡ ሸፍነህ ፡ ሰላም ፡ ሂጂ ፡ አልካት ፡ (ምሥጋናዬን)
አዝ፦ ልሰዋ ፡ የምሥጋናን ፡ መስዋዕት
ሆነኸኝ ፡ አይቻለሁ ፡ አባት
ላክብርህ ፡ እኔ ፡ ደጋግሜ
ከፍ ፡ በል ፡ ላዚም ፡ ፊትህ ፡ ቆሜ (፪x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
ገና ፡ ሌሊት ፡ ሳለ ፡ ንጋት ፡ ሳይወጋግን ፡ (ምሥጋናዬን)
ምህረትህን ፡ ሳስበው ፡ ይለኛል ፡ አመስግን ፡ (ምሥጋናዬን)
ሀሴት ፡ አደርጋለሁ ፡ በምድር ፡ በፊትህ ፡ (ምሥጋናዬን)
አንደበቴን ፡ ልክፈት ፡ ጌታ ፡ ላክብርህ ፡ (ምሥጋናዬን)
አዝ፦ ልሰዋ ፡ የምሥጋናን ፡ መስዋዕት
ሆነኸኝ ፡ አይቻለሁ ፡ አባት
ላክብርህ ፡ እኔ ፡ ደጋግሜ
ከፍ ፡ በል ፡ ላዚም ፡ ፊትህ ፡ ቆሜ (፪x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
አቤቱ ፡ ተደንቄያለሁኝና ፡ ልሰዋ ፡ ምሥጋና (፬x)
|