እለምንሃለሁ ፡ አንድ ፡ ነገር (Elemenehalehu And Neger) - ታምራት ፡ ኃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

በሳር ፡ ብንሰራ ፡ ባገዳ
ተቃጥሎብን ፡ እንዳንጎዳ
የሚያነጥር ፡ እሳት ፡ ሲመጣ
ማነው ፡ ተፈትኖ ፡ ሚወጣ

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን (፪x)

በጨለማ ፡ የተሰወረ ፡
በማስመሰል ፡ ኑሮ ፡ የኖረ
ወደ ፡ ብርሀን ፡ ታወጣለህ
ለሁሉም ፡ እንደስራው ፡ ትሰጣለህ

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን (፪x)

አንዳንዱ ፡ ለደሞዝ ፡ ይሰብካል
ሌላኛው ፡ ለጥቅም ፡ ያመልካል
ታዲያ ፡ ማነው ፡ አንተን ፡ ፈላጊ
የተናገረውን ፡ አድራጊ

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን (፪x)

ባፌ ፡ ብዙ ፡ ፍቅርን ፡ ስገልጥ
ወንድሜን ፡ በነገር ፡ ስረግጥ
ቃል ፡ አባይ ፡ ሆኜ ፡ እንዳልገኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሀሰት ፡ ጠብቀኝ

አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን (፪x)

በጓዳም ፡ ይሁን ፡ በጎዳና
ነውር ፡ የሌለባት ፡ ህሊና
በእግዚአብሄርና ፡ በሰው ፡ ፊት
እንድራመድ ፡ እርዳኝ ፡ በእውነት