ነፍሴን ፡ በፊትህ (Nefsien Befiteh) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Lyrics.jpg


(6)

ኢየሱስ ፡ ገናና ፡ ነው
(Eyesus Genana New)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 7:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)

ሊታይ ፡ በማይችል ፡ ብርሃን ፡ ውስጥ ፡ አለህ
ሠማይ ፡ ምድርን ፡ በቃል ፡ ታዛለህ
ወደደም ፡ ጠላም ፡ ፍጥረት ፡ በሙሉ
ይገዛልሃል ፡ የአንተ ፡ ነው ፡ ኃይሉ
 
አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)

ሰው ፡ ህልውናው ፡ ሞትና ፡ ሕይወቱ
ሃዘን ፡ ደስታው ፡ ሹመት ፡ ሽረቱ
ትእዛዝ ፡ ሁሉ ፡ ከአንተ ፡ ይወጣል
ክብር ፡ ላንተ ፡ እንጂ ፡ ለማን ፡ ይሰጣል?

አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)

እስከ ፡ እግርህ ፡ ጣት ፡ ዕንቁ ፡ ለብሰሃል
ወገብህንም ፡ በወርቅ ፡ ታጥቀሃል
ራስህ ፡ ነጭ ፡ ነው ፡ ዐይንህ ፡ ነበልባል
ክብርም ፡ ስግደትም ፡ ላንተ ፡ ይገባል

አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)

እግርህ ፡ በእቶን ፡ የነጠረ ፡ ናስ
ድምፅህ ፡ ያስፈራል ፡ እንደ ፡ ውቅያኖስ
የተሳለ ፡ ሰይፍ ፡ ከአፍህ ፡ ይወጣል
ከቀትር ፡ ፀሐይ ፡ ፊትህ ፡ ያበራል

አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)

ውለታህ ፡ በዝቶ ፡ ቢያስጨንቀኝ
ያለኝን ፡ ሸጬ ፡ ሽቶ ፡ ገዛሁኝ
ብልቃጡ ፡ ይሰበር ፡ ይፍሰስ ፡ በእግርህ
እንዳከበርከኝ ፡ እኔም ፡ ላክብርህ

አዝ፦ ነፍሴን ፡ በፊትህ ፡ አፈሳለሁ
እጄን ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ አነሳለሁ
ከመቀመጫዬም ፡ እወርዳለሁ
ከእግሮችህ ፡ በታች ፡ እሰግዳለሁ
አምላክ ፡ ነህና ፡ አመልክሃለሁ
ንጉሥ ፡ ነህና ፡ አነግስሃለሁ
(፪x)