እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ (Eniem Ethiopiawi Negn) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Lyrics.jpg


(6)

ኢየሱስ ፡ ገናና ፡ ነው
(Eyesus Genana New)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:58
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

አዝ፦ እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ ፡ ብዙ ፡ እንቆቅልሽ ፡ አለኝ
ጌታ ፡ አንተ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ ፡ እንቆቅልሽን ፡ መፍታት ፡ ታውቃለህ
የዕውቀት ፡ የጥበብ ፡ ጌታ ፡ እንቆቅልሼን ፡ ፍታ

በዛና ፡ እንቆቅልሼ ፡ ለብዙ ፡ ዘመን ፡ አልቅሼ
አንድ ፡ ቀን ፡ ዝናህን ፡ ሰማሁ ፡ ልነግርህ ፡ ከሳባ ፡ መጣሁ
ተቀመጥ ፡ በዙፋንህ ፡ የልቤን ፡ እንድነግርህ

አዝ፦ እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ ፡ ብዙ ፡ እንቆቅልሽ ፡ አለኝ
ጌታ ፡ አንተ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ ፡ እንቆቅልሽን ፡ መፍታት ፡ ታውቃለህ
የዕውቀት ፡ የጥበብ ፡ ጌታ ፡ እንቆቅልሼን ፡ ፍታ

በግመል ፡ ሽቱ ፡ ጭኛለሁ ወርቅና፡ ዕንቁም ፡ ይዣለሁ
ደክሞኛል ፡ ጓዜ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ አድምጠኝ ፡ ያኔ ፡ አርፋለሁ
አገሬን ፡ በዚህ ፡ ወክዬ ፡ ከእግርህ ፡ ስር ፡ ልውደቅ ፡ ጌታዬ

አዝ፦ እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ ፡ ብዙ ፡ እንቆቅልሽ ፡ አለኝ
ጌታ ፡ አንተ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ ፡ እንቆቅልሽን ፡ መፍታት ፡ ታውቃለህ
የዕውቀት ፡ የጥበብ ፡ ጌታ ፡ እንቆቅልሼን ፡ ፍታ

ሠማይና ፡ ምድርን ፡ ፈጥረሃል ፡ በጥበብህ ፡ ሁሉን ፡ አድርገሃል
ከዓይንህ ፡ የተሰወረ ፡ አሸንፎህስ ፡ የኖረ
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ኧረ ፡ ምን ፡ ነበር ፡ ፍታልኝ ፡ የእኔንም ፡ ነገር

አዝ፦ እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ ፡ ብዙ ፡ እንቆቅልሽ ፡ አለኝ
ጌታ ፡ አንተ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ ፡ እንቆቅልሽን ፡ መፍታት ፡ ታውቃለህ
የዕውቀት ፡ የጥበብ ፡ ጌታ ፡ እንቆቅልሼን ፡ ፍታ

ገና ፡ ጥንት ፡ ሳለሁ ፡ በአገሬ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ የሰማሁት ፡ ወሬ
ማመን ፡ ግን ፡ አቅቶኝ ፡ ነበር ፡ ልክ ፡ የለው ፡ የዕውቀትህ ፡ ነገር
ጥበብህ ፡ ከአእምሮ ፡ ያልፋል ፡ ከሰማሁት ፡ ዝናህ ፡ ይበልጣል

አዝ፦ እኔም ፡ ኢትዮጵያዊ ፡ ነኝ ፡ ብዙ ፡ እንቆቅልሽ ፡ አለኝ
ጌታ ፡ አንተ ፡ ንጉሥ ፡ ነህ ፡ እንቆቅልሽን ፡ መፍታት ፡ ታውቃለህ
የዕውቀት ፡ የጥበብ ፡ ጌታ ፡ እንቆቅልሼን ፡ ፍታ