Tamrat Haile/Egziabhier Terarayien Anagerew/Yajebe Sibeten

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search


አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረ በዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

አብርሃም በእምነት ቢወጣ ከኡር
ተስፋው ቢረዝምበት ገባው ጥርጥር
የተረሳ ቢመስል ዘመኑም ያለፈ
ተስፋውን ፈጸምክለት ቃልህ መች ታጠፈ

አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረበዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

እንጀራ የበላ ፈውስ የተቀበለ
ፀሐይ ቆልቆል ሲል አንድ እንኳ የታለ (፪x)
የሰው አለኝታነት ዘለቄታ የለው
በሆሳእና ማግስት ስቀለው ስቀለው (፪x)

አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረ በዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

ኑሃሚን በሞአብ ህይወት ሲመራት
የልጇ ሚስት ኦርፋ ስማ ተለየቻት
ጊዜና ሁኔታ አላምር ሲላቸው
ስመው የሚለዩ ዛሬም ብዙ ናቸው (፪x)

አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረ በዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

ሳኦል ሰይፉን ሲስል በቤተ-መንግስቱ
ጋሻ ጃግሬዎቹም አብረው ሲዶልቱ (፪x)
ትልቁም ትንሹም ዳዊትን ሲያወግዝ
ማን ይሆን ዮናታን ምስኪኑን የሚያግዝ
ለምስኪኑ የሚያግዝ

አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረ በዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን

ተስፋዬ ተሟጦ ቀን የጐደለ ዕለት
ባለዕዳ ሲመኘኝ ለዳግም ባርነት (፪x)
ሰማይም ነደደ ማድጋዬን ሞላው
እዳዬ ተከፍሎ ተረፈኝ የምበላው (፪x)

አዝ
አለኝ ወዳጅ የማይከዳ
ኑሮ ቢሆን ምድረ በዳ
የቀረበ ሲርቅ ያጀበ ሲበተን
ዞር ቀና ብዬ ሳይህ አላጣሁም አንተን