From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ኑሮ ፡ ምድረበዳ
የማይደፈን ፡ ቀዳዳ
ቋጡ ፡ ጠብ ፡ አላለም ፡ ጉድጓዱም ፡ አልሞላ
አንዱን ፡ ስንሸኘው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ሌላው
እንቆቅልሹ ፡ ሺህ ፡ ችግሩም ፡ እልፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ አምነን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ ይዘን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታ ፡ ካለ ፡ እርፍ ፡ ነው
ልንደላደል ፡ ልንመቻች
ቀን ፡ ሙሉ ፡ ስንሮጥ ፡ እላይ ፡ እታች
መቼ ፡ ሞላልን ፡ እንዲህ ፡ እየጣርን
ነፍሳችን ፡ እረፍት ፡ አጥታ
ፀሐይ ፡ ማዘቅዘቋን ፡ መምሸቱን ፡ አውቀን
ወደ ፡ እግዚአብሄር ፡ ጉያ ፡ እንግባ ፡ ፈጥነን
አዝ፦ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ኑሮ ፡ ምድረበዳ
የማይደፈን ፡ ቀዳዳ
ቋጡ ፡ ጠብ ፡ አላለም ፡ ጉድጓዱም ፡ አልሞላ
አንዱን ፡ ስንሸኘው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ሌላው
እንቆቅልሹ ፡ ሺህ ፡ ችግሩም ፡ እልፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ አምነን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ ይዘን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታ ፡ ካለ ፡ እርፍ ፡ ነው
በመሸማቀቅ ፡ በሰቀቀን
በሃሩር ፡ ፀሐይ ፡ በእኩለ ፡ ቀን
ውኃ ፍለጋ ፡ ከአድማስ ፡ ወዲያ
የተጓዘችው ፡ በሰማሪያ ፡
አምስቱም ፡ ባሎቿ ፡ ያልሰጧትን ፡ ደስታ
ኢየሱስን ፡ ስታገኝ ፡ ቋጠሮዋ ፡ ተፈታ
አዝ፦ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ኑሮ ፡ ምድረበዳ
የማይደፈን ፡ ቀዳዳ
ቋጡ ፡ ጠብ ፡ አላለም ፡ ጉድጓዱም ፡ አልሞላ
አንዱን ፡ ስንሸኘው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ሌላው
እንቆቅልሹ ፡ ሺህ ፡ ችግሩም ፡ እልፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ አምነን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ ይዘን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታ ፡ ካለ ፡ እርፍ ፡ ነው
እንድንጮህ ፡ አባት ፡ አባት ፡ ብለን
እግዚአብሔር ፡ ሰጠን ፡ መንፈሱን
በሰማይም ፡ ቤት ፡ ሰርቶልናል
በቅርቡም ፡ መጥቶ ፡ ይወስደናል
ወላጅ ፡ አልባ ፡ ልጆች ፡ አይደለንም ፡ እኛ
ጌታችን ፡ በክብር ፡ ይመጣል ፡ ዳግመኛ
አዝ፦ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ኑሮ ፡ ምድረበዳ
የማይደፈን ፡ ቀዳዳ
ቋጡ ፡ ጠብ ፡ አላለም ፡ ጉድጓዱም ፡ አልሞላ
አንዱን ፡ ስንሸኘው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ሌላው
እንቆቅልሹ ፡ ሺህ ፡ ችግሩም ፡ እልፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ አምነን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ ይዘን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታ ፡ ካለ ፡ እርፍ ፡ ነው
የቤተልሔም ፡ ረሃብ ፡ ያልፋል
ወደ ፡ ሞአብስ ፡ ምን ፡ ያለፋል
ያለመጠበቅ ፡ ያለማረፍ ፡
ለመዘረፍ ፡ ነው ፡ ለመገፈፍ
እግዚአብሔር ፡ ሕዝቡን ፡ በርግጥ ፡ ይጐበኛል
ሁሉም ፡ ሰው ፡ በጊዜው ፡ ዳኝነት ፡ ያገኛል
አዝ፦ የዚህ ፡ ዓለም ፡ ኑሮ ፡ ምድረበዳ
የማይደፈን ፡ ቀዳዳ
ቋጡ ፡ ጠብ ፡ አላለም ፡ ጉድጓዱም ፡ አልሞላ
አንዱን ፡ ስንሸኘው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ሌላው
እንቆቅልሹ ፡ ሺህ ፡ ችግሩም ፡ እልፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ አምነን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታን ፡ ይዘን ፡ እርፍ ፡ ነው
ጌታ ፡ ካለ ፡ እርፍ ፡ ነው
|