Tamrat Haile/Egziabhier Awaqi New/Tamagn New Beqalu

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ=ታምራት ፡ ሃይሌ ርዕስ=ታማኝ ነው በቃሉ

ወዳጄ አብርሃም ፊቴ ተመላለስ እኔን አይገደኝም ኪዳኔን ለማደስ እድሜህ ሮጦ ሮጦ ቢደርስልህ ከጫፍ ሰማይ ምድር ያልፋል የኔ ቃል አያልፍም አዝ ታማኝ (፫x) ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

የማያልፍ ምን አለ እግዚአብሔር ከረዳ የእምነት ምንጭ ይሆናል ይሄ ምድረ በዳ ያለው ይሄድና ደግሞ ይመጣል ሌላ ግዙፉ ተራራ ይሆናል ደልዳላ አዝ

ታማኝ (፫x)

ታማኝ ነው እግዚአብሔር በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

የመለኮት አዋጅ ከመጣ

ከሰማይ

ኢየሱስ ካዘዘ ይኬዳል ውኃ ላይ ሙታን ይነሳሉ እስራት ይፈታል ቁራሹ ተባርኮ ሺዎች ይበሉታል አዝ

ታማኝ (፫x)

ታማኝ ነው እግዚአብሔር በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ጌድዮንና ባርቅ ዮፍታሄና ሳምሶን ሳሙኤልና ዳዊት ጳውሎስና ጴጥሮስ የአንበሳን አፍ ዘጉ እሳት አልበላቸው ለታማኝነቱ ምስክሮች ናቸው አዝ ታማኝ (፫x) ታማኝ ነው እግዚአብሔር በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ምድያም በረሃ በፀሐይ ቃጠሎ በቁጥቋጦ እሳት ራዕይ አቀብሎ የፈርዖንን ክንድ በመቅሰፍት አድቅቆ አሻግሮ የለም ወይ ህዝቡን አስለቅቆ አዝ

ታማኝ (፫x)

ታማኝ ነው እግዚአብሔር በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ጉድጓዱን ቆፍረህ ውኃ ስታወጣ ዞርበል የኔ ነው ባይ ምቀኛ ቢመጣ እልፍ ብለህ ቆፍር ከሰው አትጣላ ርሆቦት ይሆናል የኋላ የኋላ አዝ

ታማኝ (፫x)

ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)