Tamrat Haile/Egziabhier Awaqi New/Tamagn New Beqalu

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ: ታምራት ፡ ሃይሌ
ርዕስ: ታማኝ ነው በቃሉ

ወዳጄ አብርሃም ፊቴ ተመላለስ
እኔን አይገደኝም ኪዳኔን ለማደስ
እድሜህ ሮጦ ሮጦ ቢደርስልህ ከጫፍ
ሰማይ ምድር ያልፋል የኔ ቃል አያልፍም

አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

የማያልፍ ምን አለ እግዚአብሔር ከረዳ
የእምነት ምንጭ ይሆናል ይሄ ምድረ በዳ
ያለው ይሄድና ደግሞ ይመጣል ሌላ
ግዙፉ ተራራ ይሆናል ደልዳላ


አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

የመለኮት አዋጅ ከመጣ ከሰማይ
ኢየሱስ ካዘዘ ይኬዳል ውኃ ላይ
ሙታን ይነሳሉ እስራት ይፈታል
ቁራሹ ተባርኮ ሺዎች ይበሉታል


አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ጌድዮንና ባርቅ ዮፍታሄና ሳምሶን
ሳሙኤልና ዳዊት ጳውሎስና ጴጥሮስ
የአንበሳን አፍ ዘጉ እሳት አልበላቸው
ለታማኝነቱ ምስክሮች ናቸው


አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ምድያም በረሃ በፀሐይ ቃጠሎ
በቁጥቋጦ እሳት ራዕይ አቀብሎ
የፈርዖንን ክንድ በመቅሰፍት አድቅቆ
አሻግሮ የለም ወይ ህዝቡን አስለቅቆ


አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)

ጉድጓዱን ቆፍረህ ውኃ ስታወጣ
ዞርበል የኔ ነው ባይ ምቀኛ ቢመጣ
እልፍ ብለህ ቆፍር ከሰው አትጣላ
ርሆቦት ይሆናል የኋላ የኋላ


አዝ ...
ታማኝ (፫x)
ታማኝ ነው እግዚአብሔር ፡ በቃሉ
ሰማይ ምድር እልል ይበሉ (፪x)