Tamrat Haile/Egziabhier Awaqi New/Keber Yehunelet

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ቃሉ ሲያስተምረን መንፈሱ ሲያጽናናን
ካቻምናን አለፍን ተሻገርን ፡ አምናን
ጠላት ቢቃወመን እጅግ ተገዳድሮ
ጌታ ተዋግቶልን ደረስን ዘንድሮ (፪x)


አዝ ተራራ ፡ የሚናድለት ፡ ጨለማ ፡ ሚገፈፍለት
ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት
ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁንለት


መጻተኞች ብንሆን ምድር ያልተገባን
ምንም አልጐደለን ለእኛ ከሚረባን
ወላጅ እንደሌለው ልጅ አላደረገን
የሁላችን አባት እግዚአብሔር ይመስገን (፪x)


አዝ ተራራ የሚናድለት ጨለማ ሚገፈፍለት
ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ፡ ሚታዘዝለት
ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁን


ጉንድሹ ቢመጣ ፡ አካሉ ፡ ተሟልቶ
እውሩ ቢመጣ ሄደ ዓይኑ ተከፍቶ
ሙታን ተነስተዋል የተራቡም በሉ
እጁን ከዘረጋ ይደርሳል ለሁሉ (፪x)


አዝ ተራራ የሚናድለት ጨለማ ሚገፈፍለት
ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት
ኢየሱስ ኢየሱስ ክብርp ይሁንለት


ሕዝቡ እንደሆነ አይቀር ተስፋውን መውረሱ
ፈርዖን ለምን ነው ኃይሉን መጨረሱ
ባሕር ተከፈለ በድል ተሻገሩ
አንዴ እስከዘለዓለም ተሰብሯል ቀንበሩ (፪x)


አዝ ተራራ ፡ የሚናድለት ፡ ጨለማ ፡ ሚገፈፍለት
ነፋሳት የሚገዙለት ወጀቡ ሚታዘዝለት
ኢየሱስ ኢየሱስ ክብር ይሁንለት ።