እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው (Egziabhier Awaqi New) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

 
አዝ:- እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው ፡ አዋቂ ፡ ነው (፪x)
ስራችንን ፡ ይመዝናል ፡ ዋጋችንን ፡ ይተምናል
ከፋኝ ፡ ብለን ፡ አናጉረምርም ፡ ስለሁሉ ፡ እናመስግነው
ደላኝ ፡ ብለን ፡ አንታበይ ፡ እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው

ቃልን ፡ ለመናገር ፡ አንደበት ፡ ቸኩሎ
ሲያነሳ ፡ ሲጥል ፡ ባልዋሉበት ፡ ውሎ
ለምን ፡ እናፍራለን ፡ በተናገርንበት
እርሱ ፡ ያደላድላል ፡ ሁሉንም ፡ ተውለት

ሃሰት ፡ ሲሆን ፡ እውነት ፡ ያልነው
ጸድቆ ፡ ሲገኝ ፡ የኮንነው
አንተ ፡ ያልነው ፡ ሲሆን ፡ አንቱ
ለእኛ ፡ ሚቀረን ፡ ትዝብቱ

አዝ:- እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው ፡ አዋቂ ፡ ነው (፪x)
ስራችንን ፡ ይመዝናል ፡ ዋጋችንን ፡ ይተምናል
ከፋኝ ፡ ብለን ፡ አናጉረምርም ፡ ስለሁሉ ፡ እናመስግነው
ደላኝ ፡ ብለን ፡ አንታበይ ፡ እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው

ፍሬ ፡ የሌለባት ፡ የደረቀች ፡ ዛፍ
እያሉ ፡ ገረፏት ፡ ስታገድም ፡ ስታልፍ
ኋላም ፡ ሰባት ፡ ወልዳ ፡ ምስኪን ፡ መካኒቱ
የተባለው ፡ ሁሉ ፡ መና ፡ ሲሆን ፡ ከንቱ

ልዑል ፡ አምላክ ፡ ከፍ ፡ ሲያደርጋት
ቢንጠራሩ ፡ ላይደርሱባት
አዋቂ ፡ ነው ፡ እግዚአብሔር
ብላ ፡ ተቀኘች ፡ በመዝሙር

አዝ:- እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው ፡ አዋቂ ፡ ነው (፪x)
ስራችንን ፡ ይመዝናል ፡ ዋጋችንን ፡ ይተምናል
ከፋኝ ፡ ብለን ፡ አናጉረምርም ፡ ስለሁሉ ፡ እናመስግነው
ደላኝ ፡ ብለን ፡ አንታበይ ፡ እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው

ፈተና ፡ በዝቶብን ፡ ብናዝን ፡ ብንከፋ
ቢወሳሰብብን ፡ ውሉ ፡ እስከሚጠፋ
ሚስጥሩ ፡ የአምላክ ፡ ነው ፡ ሁሉም ፡ ነገር ፡ በእጁ
የተገለጠው ፡ ግን ፡ ለእኛ ፡ ለልጆቹ

ሁሉን ፡ ሲያደርግ ፡ የለን ፡ በጐ
ሲያበጃጀው ፡ ውብ ፡ አድርጐ
እናያለን ፡ የእርሱን ፡ ማዳን
እንድንጸና ፡ ጌታ ፡ ይርዳን

አዝ:- እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው ፡ አዋቂ ፡ ነው (፪x)
ስራችንን ፡ ይመዝናል ፡ ዋጋችንን ፡ ይተምናል
ከፋኝ ፡ ብለን ፡ አናጉረምርም ፡ ስለሁሉ ፡ እናመስግነው
ደላኝ ፡ ብለን ፡ አንታበይ ፡ እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው