አቀበት ፡ ሜዳ (Aqebet Meda) - ታምራት ፡ ሃይሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታምራት ፡ ሃይሌ
(Tamrat Haile)

Lyrics.jpg

፲ ፩
(11)

በድብብቆሽ ፡ ቀኑ ፡ እንዳያልፍ
(Bedebebeqosh Qenu Endayalf)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:48
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታምራት ፡ ሃይሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Tamrat Haile)

አቀበት ፡ ሜዳ ፡ ገደላ ፡ ገደል
የታለፈበት ፡ የሚረሳ ፡ አይደል
ነዳፊው ፡ እባብ ፡ ነካሹ ፡ አውሬ
ስንት ፡ አስረገጠኝ ፡ በዚህ ፡ በእግሬ
የሠማይ ፡ አምላክ ፡ አቤት ፡ ምህረቱ
ማድረግ ፡ ይችላል፡ ደካማን ፡ ብርቱ
በእርሱ ፡ ሆናችሁ ፡ ያያችሁ ፡ ብዙ
በዕልልታ ፡ ሆታ ፡ ምሥጋናን ፡ አብዙ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ
መካሪ ፡ ወንድም ፡ ወላጅ ፡ አባቴ
የሆነልኝ ፡ ሁሉ ፡ በሁሉ
ቆርቁሮኝ ፡ አያውቅ ፡ ጠባይ ፡ አመሉ

ጣቱን ፡ በመያዝ ፡ ዳዴ ፡ ተምሬ
ቆሜ ፡ ለመሄድ ፡ ሆኖልኝ ፡ ዛሬ
የጥንቱ ፡ አምላክ ፡ የልጅነቴ
ዛሬም ፡ ላክብረው ፡ በአንደበቴ

ይሄ ፡ ክፉ ፡ ዓለም ፡ ምኑ ፡ ይመቻል
በሥጋ ፡ በደም ፡ የትኛው ፡ ሲቻል
በየማለዳው ፡ አዲስ ፡ በሆነው
በምህረቱ ፡ ነው ፡ ያልጠፋነው
እንደ ፡ እኔ ፡ ቢሆን ፡ እንደድካሜ
ዛሬም ፡ በፊቱ ፡ ባልታየሁ ፡ ቆሜ
በዓይኔ ፡ እያየሁት ፡ አለፈ ፡ ስንቱ
የያዘኝ ፡ አምላክ ፡ እግዚአብሔር ፡ ብርቱ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ
መካሪ ፡ ወንድም ፡ ወላጅ ፡ አባቴ
የሆነልኝ ፡ ሁሉ ፡ በሁሉ
ቆርቁሮኝ ፡ አያውቅ ፡ ጠባይ ፡ አመሉ

ጣቱን ፡ በመያዝ ፡ ዳዴ ፡ ተምሬ
ቆሜ ፡ ለመሄድ ፡ ሆኖልኝ ፡ ዛሬ
የጥንቱ ፡ አምላክ ፡ የልጅነቴ
ዛሬም ፡ ላክብረው ፡ በአንደበቴ

ይህን ፡ ዮርዳኖስን ፡ ስሻገረው
ደረቅ ፡ በትር ፡ ነው ፡ በእጄ ፡ የነበረው
ዛሬ ፡ ግን ፡ ይሄው ፡ ዓለመለኝ
በተዓምራቱ ፡ እያስገረመኝ
ሕይወት ፡ ዥንጉርጉር ፡ ቀለሙ ፡ ብዙ
መች ፡ ቀላል ፡ ሆነ ፡ ጓዙ ፡ መዘዙ
የሰበሰበኝ ፡ የያዘኝ ፡ ጌታ
ስሙ ፡ ከፍ ፡ ይበል ፡ በዕልልታ ፡ ሆታ

አዝ፦ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መድሃኒቴ
መካሪ ፡ ወንድም ፡ ወላጅ ፡ አባቴ
የሆነልኝ ፡ ሁሉ ፡ በሁሉ
ቆርቁሮኝ ፡ አያውቅ ፡ ጠባይ ፡ አመሉ

ጣቱን ፡ በመያዝ ፡ ዳዴ ፡ ተምሬ
ቆሜ ፡ ለመሄድ ፡ ሆኖልኝ ፡ ዛሬ
የጥንቱ ፡ አምላክ ፡ የልጅነቴ
ዛሬም ፡ ላክብረው ፡ በአንደበቴ