From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርጌ ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
ከወህኒ ፡ ከፍርድ ፡ እኔኑ ፡ ሊያወጣ
ከድንግል ፡ ማርያም ፡ ሥጋ ፡ ለብሶ ፡ መጣ
መልክ ፡ ውበቱን ፡ ተወ ፡ የባርያን ፡ መልክ ፡ ያዘ
እስከ ፡ መስቀል ፡ ሞት ፡ በፍቅር ፡ ታዘዘ
ከአደረገው ፡ በቀር ፡ ኢየሱሴ ፡ ምንም ፡ ታሪክ ፡ የለኝ ፡ የእራሴ
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
በቃሉ ፡ እውነተኛ ፡ በተግባሩም ፡ ደግ
ከፋት ፡ የሌለበት ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
እኔን ፡ ሊያዘምረኝ ፡ እርሱ ፡ አለቀሰ
እኔን ፡ ሊያከብረኝ ፡ ።ውረትን ፡ ለበሰ
ከሥም ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ሥም ፡ አለው
ዛሬም ፡ ምሥጋናዬ ፡ ለእርሱ ፡ ነው
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
ብዙ ፡ የነበረውን ፡ እዳዬን ፡ ሻረልኝ
ኃጢአቴን ፡ ሁሉ ፡ ከኋላው ፡ ጣለልኝ
በመስቀል ፡ ጠርጐ ፡ ከእኔ ፡ አስወግዶ
ጨካኙን ፡ ከሳሼን ፡ ባዶ ፡ እጁን ፡ ሰደደው
እዛጋ ፡ ጀመረ ፡ ታሪኬ ፡ ምሥጋና ፡ ይብዛለት ፡ አምላኬ
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ (፪x)
|