From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው
በመስቀሉ ግርጌ
በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ
ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ
ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ
ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ
ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ
ከወህኒ ከፍርድ እኔኑ ሊያወጣ
ከድንግል ማርያም ሥጋ ለብሶ መጣ
መልክ ውበቱን ተወ የባርያን መልክ ያዘ
እስከ መስቀል ሞትም በፍቅር ታዘዘ
ካደረገው በቀር ኢየሱሴ
ምንም ታሪክ የለኝ የእራሴ
አዝ
ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው
በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ
ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ
ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ
ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ
ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ
በቃሉ እውነተኛ በተግባሩም ደግ
ከፋት የሌለበት የእግዚአብሔር በግ
እኔን ሊያዘምረኝ እርሱ አለቀሰ
እኔኑ ሊያከብረኝ ውርደትን ለበሰ
ከሥም ሁሉ በላይ ሥም አለው
ዛሬም ምሥጋናዬ ለእርሱ ነው
አዝ
ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው
በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ
ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ
ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ
ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ
ይሄ ውብ በታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ
ብዙ የነበረውን እዳዬን ሻረልኝ
ኃጢአቴን ሁሉ ከኋላው ጣለልኝ
በመስቀል ጠርቆ ከእኔ አስወግደው
ጨካኙን ከሳሼን ባዶ እጁን ሰደደው
እዚያው ጋ ጀመረ ታሪኬ
ምሥጋና ይብዛለት አምላኬ
አዝ
ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው
በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ
ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ
ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ
ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ
ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ (፪x)
|