Tamrat Haile/Ahunem Alehu Bemerkebu/Tarikie Yejemerew

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ታምራት ሃይሌ ርዕስ ታሪኬ የጀመረው አልበም አሁንም አለሁ በመርከቡ

ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ

ከወህኒ ከፍርድ እኔኑ ሊያወጣ ከድንግል ማርያም ሥጋ ለብሶ መጣ መልክ ውበቱን ተወ የባርያን መልክ ያዘ እስከ መስቀል ሞትም በፍቅር ታዘዘ ካደረገው በቀር ኢየሱሴ ምንም ታሪክ የለኝ የእራሴ

አዝ ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ

በቃሉ እውነተኛ በተግባሩም ደግ ከፋት የሌለበት የእግዚአብሔር በግ እኔን ሊያዘምረኝ እርሱ አለቀሰ እኔኑ ሊያከብረኝ ውርደትን ለበሰ ከሥም ሁሉ በላይ ሥም አለው ዛሬም ምሥጋናዬ ለእርሱ ነው

አዝ ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ ይሄ ውብ በታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ

ብዙ የነበረውን እዳዬን ሻረልኝ ኃጢአቴን ሁሉ ከኋላው ጣለልኝ በመስቀል ጠርቆ ከእኔ አስወግደው ጨካኙን ከሳሼን ባዶ እጁን ሰደደው እዚያው ጋ ጀመረ ታሪኬ ምሥጋና ይብዛለት አምላኬ

አዝ ታሪኬ የጀመረው በቀራኒዮ ነው በመስቀሉ ግርጌ በአጋጣሚ አይደለም መወለድ ማደጌ ሠይጣን ሲቀጠቀጥ እራሱን ሲመታ ባርነቴ ሲሻር ሰንሰለት ሲፈታ ጠላት ሲመሽበት ለእኔ ግን ሲነጋ ይሄ ውብ ታሪኬ ተጀመረ እዚያጋ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው ለጌታዬ ምሥጋናዬ ምሥጋናዬ ይኼው በዜማዬ (፪x)