From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
አዝ፦
ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡
በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርጌ ፡
በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡
መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡
እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡
ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡
ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡
ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
ከወህኒ ፡ ከፍርድ ፡
እኔኑ ፡ ሊያወጣ
ከድንግል ፡ ማርያም ፡
ሥጋ ፡ ለብሶ ፡ መጣ
መልክ ፡ ውበቱን ፡ ተወ ፡
የባርያን ፡ መልክ ፡ ያዘ
እስከ ፡ መስቀል ፡ ሞት ፡ በፍቅር ፡ ታዘዘ
ከአደረገው ፡ በቀር ፡ ኢየሱሴ ፡ ምንም ፡ ታሪክ ፡ የለኝ ፡ የእራሴ
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
በቃሉ ፡ እውነተኛ ፡
በተግባሩም ፡ ደግ
ከፋት ፡ የሌለበት ፡
የእግዚአብሔር ፡ በግ
እኔን ፡ ሊያዘምረኝ ፡ እርሱ ፡ አለቀሰ
እኔን ፡ ሊያከብረኝ ፡ ። ውረደትን ፡ ለበሰ
ከሥም ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ሥም ፡ አለው
ዛሬም ፡ ምሥጋናዬ ፡ ለእርሱ ፡ ነው
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ
ብዙ ፡ የነበረውን ፡
እዳዬን ፡ ሻረልኝ
ኃጢአቴን ፡ ሁሉ ፡ ከኋላው ፡ ጣለልኝ
በመስቀል ፡ ጠርጐ ፡
ከእኔ ፡ አስወግዶ
ጨካኙን ፡ ከሳሼን ፡
ባዶ ፡ እጁን ፡ ሰደደው
እዛጋ ፡ ጀመረ ፡ ታሪኬ ፡
ምሥጋና ፡ ይብዛለት ፡ አምላኬ
አዝ፦ ታሪኬ ፡ የጀመረው ፡ በቀራኒዮ ፡ ነው
በመስቀሉ ፡ ግርግር ፡ በአጋጣሚ ፡ አይደለም ፡ መወለድ ፡ ማደጌ
ሠይጣን ፡ ሲቀጠቀጥ ፡ እራሱን ፡ ሲመታ
ባርነቴ ፡ ሲሻር ፡ ሰንሰለት ፡ ሲፈታ
ጠላት ፡ ሲመሽበት ፡ ለእኔ ፡ ግን ፡ ሲነጋ
ኢኸው ፡ በታሪኬ ፡ ተጀመረ ፡ እዚያጋ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ ለጌታዬ
ምሥጋናዬ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ይኼው ፡ በዜማዬ (፪x)
|