From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ሰዶም ፡ ገሞራ (፬x)
ሰው ፡ እግዚአብሔርን ፡ አይፈራ
ሰዶም ፡ ገሞራ
ግርግር ፡ ነው ፡ ከተማው
አንዱ ፡ ሌላውን ፡ አይሰማው
ሁሉም ፡ ይሮጣል ፡ ለንግዱ
ጐዳናው ፡ ጠቧል ፡ መንገዱ
ለነፍሱ ፡ አያስብ ፡ ለሰማይ ፡ ቤቱ
ለዛሬ ፡ ብቻ ፡ ለለት ፡ ለለቱ
አዝ፦ ሰዶም ፡ ገሞራ (፬x)
ሰው ፡ እግዚአብሔርን ፡ አይፈራ
ሰዶም ፡ ገሞራ
ወንድ ፡ ከወንድ ፡ ጋብቻ
ሴትም ፡ ከሴት ፡ ጋር ፡ ጋብቻ
በፍትወት ፡ እሳት ፡ ሲቃጠል
ሲጋደም ፡ በየስርቻ
እንሰሳ ፡ ሆነ ፡ አዬ! ፡ ክቡር ፡ ሰው
መድኋኒት ፡ የለሽ ፡ ደዌ ፡ ጨረሰው
አዝ፦ ሰዶም ፡ ገሞራ (፬x)
ሰው ፡ እግዚአብሔርን ፡ አይፈራ
ሰዶም ፡ ገሞራ
ሕጻን ፡ አይሉ ፡ አዋቂ
አንዱ ፡ በሌላው ፡ ሸማቂ
ቀድሞ ፡ ጣዩ ፡ አልታወቀ ፡ እንጂ
ሰው ፡ ሁሉ ፡ ጨብጧል ፡ ፈንጂ
የፍቅር ፡ ኑሮ ፡ የዕርቅ ፡ ሰላም
ክፋት ፡ ጠረገው ፡ ጠፋ ፡ ካለም
አዝ፦ ሰዶም ፡ ገሞራ (፬x)
ሰው ፡ እግዚአብሔርን ፡ አይፈራ
ሰዶም ፡ ገሞራ
ልጅ ፡ የናቱን ፡ ሆድ ፡ ረገጠ
አባት ፡ ልጁን ፡ ገላመጠ
እናትም ፡ ጣለች ፡ ልጇን
ቀረቀረችው ፡ ደጇን
ጣራው ፡ ዘበጠ ፡ ቤቱ ፡ ተናጋ
ዳኛ ፡ ጠፋና ፡ የሚያረጋጋ
አዝ፦ ሰዶም ፡ ገሞራ (፬x)
ሰው ፡ እግዚአብሔርን ፡ አይፈራ
ሰዶም ፡ ገሞራ
|