From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
ተሳፍሬአለሁ ፡ በባቡሩ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከሰፈሩ
መቆም ፡ አልሻም ፡ በመንገዱ
ይቆራርጣል ፡ ሐዲዱ
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
ስንቶች ፡ ተጓዙ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ
ሸለቆ ፡ ወርደው ፡ ወጡ ፡ ተራራ
እየመሰለኝ ፡ ከጐኔ ፡ እያሉ
እኔ ፡ መች ፡ አወቅሁ ፡ እንደተበሉ
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
ሳይመርምሩ ፡ ጊዜ ፡ ዘመኑን
ሳያውቁት ፡ ውኋው ፡ ጥልቅ ፡ መሆኑን
መንሸራሸር ፡ እያማራቸው
ሳያውቁት ፡ ድንገት ፡ ውጦ ፡ አስቀራቸው
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
ስንቱን ፡ አልፌ ፡ እዚህ ፡ መድረሴ
በፀጋው ፡ እንጂ ፡ መቼ ፡ በራሴ
ጌታ ፡ ሰጥቶኛል ፡ አቅሜን ፡ መለኪያ
ከፀጋው ፡ በቀር ፡ ያለኝ ፡ መመኪያ
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
መርከቡ ፡ ሲቆም ፡ በየወደቡ
ወራጁን ፡ ሲያወርድ ፡ ሌሎች ፡ ሲገቡ
በየከተማው ፡ ባቡሩም ፡ ሲያልፍ
እንዱን ፡ ሲያሳፍር ፡ ሌላውን ፡ ሲያራግፍ
ከጫፍ ፡ የሚደርስ ፡ ማን ፡ ይሆን ፡ እንጃ
አጽናኝ ፡ እያልኩኝ ፡ ይዣለሁ ፡ ምልጃ
አዝ፦ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ
ገና ፡ አልደረሰም ፡ ከወደቡ
መውረድ ፡ አልሻም ፡ እጓዛለሁ
ውኋ ፡ እንዳይበላኝ ፡ እፈራለሁ
|