Tamrat Haile/Ahunem Alehu Bemerkebu/Ahunem Alehu Bemerkebu
ዘማሪ ታምራት ሃይሌ ርዕስ አሁንም አለሁ በመርከቡ አልበም አሁንም አለሁ በመርከቡ
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ተሳፍሬአለሁ በባቡሩ ገና አልደረሰም ከሰፈሩ መቆም አልሻም በመንገዱ ይቆራርጣል ሐዲዱ
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ስንቶች ተጓዙ ከእኔ ጋራ ሸለቆ ወርደው ወጡ ተራራ እየመሰለኝ ከጐኔ እያሉ እኔ መች አወቅሁ እንደተበሉ
አዝ አሁንም ፡ አለሁ ፡ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ሳይመርምሩ ጊዜ ዘመኑን ሳያውቁት ውኋው ጥልቅ መሆኑን መንሸራሸር እያማራቸው ሳያውቁት ድንገት ውጦ አስቀራቸው
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ስንቱን አልፌ እዚህ መድረሴ በፀጋው እንጂ መቼ በራሴ ጌታ ሰጥቶኛል አቅሜን መለኪያ ከፀጋው በቀር ያለኝ መመኪያ
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
መርከቡ ሲቆም በየወደቡ ወራጁን ሲያወርድ ሌሎች ሲገቡ በየከተማው ባቡሩም ሲያልፍ እንዱን ሲያሳፍር ሌላውን ሲያራግፍ ከጫፍ የሚደርስ ማን ይሆን እንጃ አጽናኝ እያልኩኝ ይዣለሁ ምልጃ
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ