Tamrat Haile/Ahunem Alehu Bemerkebu/Ahunem Alehu Bemerkebu
ዘማሪ ታምራት ሃይሌ
ርዕስ አሁንም አለሁ በመርከቡ
አልበም አሁንም አለሁ በመርከቡ
አዝ
አሁንም አለሁ በመርከቡ
ገና አልደረሰም ከወደቡ
መውረድ አልሻም እጓዛለሁ
ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ተሳፍሬአለሁ በባቡሩ
ገና አልደረሰም ከሰፈሩ
መቆም አልሻም በመንገዱ
ይቆራርጣል ሐዲዱ
አዝ
አሁንም አለሁ በመርከቡ
ገና አልደረሰም ከወደቡ
መውረድ አልሻም እጓዛለሁ
ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ስንቶች ተጓዙ ከእኔ ጋራ
ሸለቆ ወርደው ወጡ ተራራ
እየመሰለኝ ከጐኔ እያሉ
እኔ መች አወቅሁ እንደተበሉ
አሁንም አለሁ በመርከቡ
ገና አልደረሰም ከወደቡ
መውረድ አልሻም እጓዛለሁ
ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ሳይመርምሩ ጊዜ ዘመኑን
ሳያውቁት ውኋው ጥልቅ መሆኑን
መንሸራሸር እያማራቸው
ሳያውቁት ድንገት ውጦ አስቀራቸው
አዝ አሁንም አለሁ በመርከቡ ገና አልደረሰም ከወደቡ መውረድ አልሻም እጓዛለሁ ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
ስንቱን አልፌ እዚህ መድረሴ
በፀጋው እንጂ መቼ በራሴ
ጌታ ሰጥቶኛል አቅሜን መለኪያ
ከፀጋው በቀር የለኝ መመኪያ
አሁንም አለሁ በመርከቡ
ገና አልደረሰም ከወደቡ
መውረድ አልሻም እጓዛለሁ
ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ
መርከቡ ሲቆም በየወደቡ
ወራጁን ሲያወርድ ሌሎች ሲገቡ
በየከተማው ባቡሩም ሲያልፍ
እንዱን ሲያሳፍር ሌላውን ሲያራግፍ
ከጫፍ የሚደርስ ማን ይሆን እንጃ
አጽናኝ እያልኩኝ ይዣለሁ ምልጃ
አሁንም አለሁ በመርከቡ
ገና አልደረሰም ከወደቡ
መውረድ አልሻም እጓዛለሁ
ውኋ እንዳይበላኝ እፈራለሁ