አምላኬን ፡ ሁልጊዜ ፡ እባርከዋለሁ (Amlakien Hulgizie Ebarekewalehu) - ታጋይ ፡ ወልደማርያም

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታጋይ ፡ ወልደማርያም
(Tagay Woldemariam)

Lyrics.jpg


(1)

ብዙ ፡ ዘመን ፡ የተሸከመኝ
(Bezu Zemen Yeteshekemegn)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 6:01
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታጋይ ፡ ወልደማርያም ፡ አልበሞች
(Albums by Tagay Woldemariam)

አዝ፦ አምላኬን ፡ ሁልጊዜ ፡ አባርከዋለሁ
ምሥጋናው ፡ ዘወተር ፡ ዘወትር ፡ በአፌ ፡ ነው (፪x)

በጠዋት ፡ በማታ ፡ በቀን ፡ በሌሊት
ምሥጋናዬ ፡ ይድረስ ፡ ዘወትር ፡ በእርሱ ፡ ፊት
የአንደበቴን ፡ ፍሬ ፡ ከቶ ፡ አልቆጥብም
ብዙ ፡ አድርጐልኛል ፡ አሃሃ ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ አልልም

አዝ፦ አምላኬን ፡ ሁልጊዜ ፡ አባርከዋለሁ
ምሥጋናው ፡ ዘወትር ፡ ዘወትር ፡ በአፌ ፡ ነው (፪x)

የሕይወቴ ፡ ጋሻ ፡ ተገን ፡ ሆኖልኛል
ስወጣም ፡ ሰገባም ፡ እረፍቱ ፡ ከቦኛል
እርሱን ፡ ለማመስገን ፡ በገናዬን ፡ ላንሳ
ያደረገልኝን ፡ በፍፁም ፡ ሳልረሳ

አዝ፦ አምላኬን ፡ ሁልጊዜ ፡ አባርከዋለሁ
ምሥጋናው ፡ ዘወትር ፡ ዘወትር ፡ በአፌ ፡ ነው (፪x)

ስላደረገልኝ ፡ እጅግ ፡ ብዙ ፡ ውለታ
አመልከዋለሁኝ ፡ ሳልሰለች ፡ ለአንድ ፡ አፍታ
ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ምለው ፡ ምሰጠው ፡ የለኝም
ዘምርለታለሁ ፡ እኔስ ፡ እስከ ፡ ዘለዓለም

አዝ፦ አምላኬን ፡ ሁልጊዜ ፡ አባርከዋለሁ
ምሥጋናው ፡ ዘወትር ፡ ዘወትር ፡ በአፌ ፡ ነው (፪x)

አቻምናን ፡ ማለፌ ፡ ሲደንቀኝ
አምናን ፡ በምህረትህ ፡ አለፍኩኝ
ለዘንድሮም ፡ ቢሆን ፡ አልፈራም
ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነህ ፡ አልሰጋም (፫x)
ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነህ ፡ አልሰጋም (፫x)
ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነህ ፡ አልሰጋም

እጅግ ፡ ብዙ ፡ ውለታ ፡ ለነፍሴ
አድርገህላታል ፡ ኢየሱሴ (፪x)

አሳቤን ፡ ጭንቀቴን ፡ ወስደሃል
አምላኬ ፡ አሳርፈኸኛል
በሕይወቴ ፡ ልትኖር ፡ መርጠሃል
የእኔንም ፡ ምሥጋና ፡ ወድሃል (፪x)
የእኔንም ፡ ምሥጋና ፡ ወደሃል ፡ መርጠሃል ፡ መርጠሃል
የእኔንም ፡ አምልኮ ፡ መርጠሃል

እጅግ ፡ ብዙ ፡ ውለታ ፡ ለነፍሴ
አድርገህላታል ፡ ኢየሱሴ (፮x)