እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት (Egziabhier Yetewagalet) - ታደሰ ፡ መኩሪያ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታደሰ ፡ መኩሪያ
(Tadesse Mekuria)

Tadesse Mekuria 2.png


(2)

ታማኝ ፡ ነው ፡ እግዚአብሔር
(Tamagn New Egziabhier)

ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታደሰ ፡ መኩሪያ ፡ አልበሞች
(Albums by Tadesse Mekuria)

አዝ፦ ማነው ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት?
ከፊቱ ፡ ወጥቶ ፡ ጠላትን ፡ ሁሉ ፡ ድል ፡ የነሳለት
ዝም ፡ ያሰኘለት?

ተራራ ፡ ላይ ፡ ሆኖ ፡ ጠላቴ ፡ ሲፎክር
የማይወድቅ ፡ መስሎት ፡ ሕይወቴን ፡ ሲያሸብር
በሰማይ ፡ የሚኖር ፡ አምላክ ፡ የሆነው
ከከፍታ ፡ አውርዶ ፡ በእግሬ ፡ ሥር ፡ ጣለው

አዝ፦ ማነው ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት?
ከፊቱ ፡ ወጥቶ ፡ ጠላትን ፡ ሁሉ ፡ ድል ፡ የነሳለት
ዝም ፡ ያሰኘለት?

ዘወትር ፡ ዕንቅፋትን ፡ በፊቴ ፡ ላይ ፡ ሲያኖር
ከበነዋል ፡ በቃ ! እያለ ፡ ሲፎክር
መብረቁን ፡ ልኮ ፡ ጌታ ፡ አወካቸው
ዳግም ፡ ላይነሱ ፡ በጥልቅ ፡ ጣላቸው

አዝ፦ ማነው ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት?
ከፊቱ ፡ ወጥቶ ፡ ጠላትን ፡ ሁሉ ፡ ድል ፡ የነሳለት
ዝም ፡ ያሰኘለት?

ነበረብኝ ፡ ብዙ ፡ ሸክም ፡ የሆነብኝ
ልቤንም ፡ አቅልጦት ፡ በጣም ፡ ያስጨነቀኝ
ጌታ ፡ ደርሶልኝ ፡ እኔን ፡ አስጥሎኛል
በቅዱሱ ፡ ማደሪያው ፡ እንዳርፍ ፡ እረድቶኛል

አዝ፦ ማነው ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት?
ከፊቱ ፡ ወጥቶ ፡ ጠላትን ፡ ሁሉ ፡ ድል ፡ የነሳለት
ዝም ፡ ያሰኘለት?

እንደዚህ ፡ እረድቶኝ ፡ ከጠላት ፡ ድኛለሁ
በማያልቅ ፡ ፍቅሩ ፡ ጸንቼ ፡ ቆሜያለሁ
ከእንግዲህ ፡ በቃ ፡ ጌታ ፡ ይቀድመኛል
ስለሚዋጋልኝ ፡ ማክበር ፡ ይገባኛል

አዝ፦ ማነው ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ እግዚአብሔር ፡ የተዋጋለት?
ከፊቱ ፡ ወጥቶ ፡ ጠላትን ፡ ሁሉ ፡ ድል ፡ የነሳለት
ዝም ፡ ያሰኘለት?