እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም (Ende Egziabhier Yale Manem Yelem) - ታደሰ ፡ እሸቴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ታደሰ ፡ እሸቴ
(Tadesse Eshete)

Lyrics.jpg


(1)

የታረደው ፡ በግ
(Yetaredew Beg)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:59
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የታደሰ ፡ እሸቴ ፡ አልበሞች
(Albums by Tadesse Eshete)

ሰው ፡ ሁኔታን ፡ አይቶ ፡ ይከዳል
ጊዜን ፡ ጠብቆ ፡ ይርቃል
ተስፋ ፡ እንደሌለው ፡ የማይተው
ጌታዬ ፡ እግዚአብሔር ፡ ብቻ ፡ ነው
ዕውቀትን ፡ አይቶ ፡ ይከዳል
አላፊ ፡ መሆኑን ፡ ዘንግቷል
እያየ ፡ የአሁን ፡ የአሁኑን
ረስቶ ፡ አወዳደቄን

አዝ፦ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም (፪x)
ዘለዓለም (፪x)

ትካዜዬን ፡ ለእርሱ ፡ ጥዬ
የውስጤን ፡ መቃተት ፡ ጌታዬ
ሰው ፡ እንኳን ፡ ቢከዳ ፡ ቢጥል
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ይረዳል
ሃሳቤን ፡ የሚያውቅልኝ
ድካሜን ፡ የሚረዳልኝ
የውስጥ ፡ ጭንቀቴ ፡ የሚገባው
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማነው?

አዝ፦ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም (፪x)
ዘለዓለም (፪x)

አጽናኝ ፡ መስሎ ፡ ይጠጋል
ጓደኛ ፡ መስሎ ፡ ይቀርባል
ጠላትም ፡ በእርሱ ፡ ተጠቅሞ
ብርሃኔንም ፡ አጨልሞ
ግን ፡ የሚመካው ፡ የምጠጋው
የልቤን ፡ የማጫውተው
ድጋፍ ፡ መከታ ፡ የማደርገው
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማነው?

አዝ፦ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም (፪x)
ዘለዓለም (፪x)