በሞቱ ፡ አዳነኝ (Bemotu Adanegn) - ሰለሞን ፡ ይርጋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሰለሞን ፡ ይርጋ
(Solomon Yirga)

Solomon Yirga 1.png


(1)

ይገርማል
(Yegermal)

ዓ.ም. (Year): 2005
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሰለሞን ፡ ይርጋ ፡ አልበሞች
(Albums by Solomon Yirga)

 
እውነቱ ፡ አዳነኝ ፡ እውነት ፡ ነው
ፈልጐ ፡ አገኘኝ ፡ ፍቅር ፡ ነው
አደራረጉ ፡ ልዩ ፡ ነው
ከምንገምተው ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

እኔ ፡ ልናገር ፡ ተደርጐልኛል
ቀንበሬም ፡ በርሱ ፡ ተሰብሮልኛል
አርነት ፡ ወጣሁ ፡ ነፃ ፡ አውጥቶኛል
ከዚያች ፡ ሩጫ ፡ እኔን ፡ ፈቶኛል

የተፈታ ፡ ሰው ፡ የተለቀቀ
መውጣት ፡ መግባቱ ፡ የተጠበቀ
ያመሰግናል ፡ ያመሰግናል ፡ ጊዜው ፡ ሁኔታ ፡ መች ፡ ያስቆመዋል
ያመሰግናል ፡ ያመሰግናል ፡ ማግኘት ፡ ማጣቱ ፡ መች ፡ ያስቆመዋል

ያኔ ፡ በልጅነት ፡ ገና ፡ መጀመሪያ
ጌታ ፡ ተናገረኝ ፡ በኔ ፡ እንደሚሰራ
የተናገረው ፡ ቃል ፡ ጊዜውን ፡ ጠብቆ
ሲፈጸም ፡ በዓይኔ ፡ አየሁ ፡ ጌታ ፡ አይረሳም ፡ እኮ (፪x)

አንድ ፡ የገባኝ ፡ ነገር ፡ የተረዳሁት
እንደማይረሳ ፡ ነው ፡ በዘመኔ ፡ ያየሁት
አንድ ፡ የገባኝ ፡ ነገር ፡ የተረዳሁት
እንደማይጥል ፡ ነው ፡ በዘመኔ ፡ ያየሁት

አንድ ፡ የገባኝ ፡ ነገር ፡ የተረዳሁት
ረዳት ፡ መሆኑን ፡ ነው ፡ በዘመኔ ፡ ያየሁት
አንድ ፡ የገባኝ ፡ ነገር ፡ የተረዳሁት
ትልቅነቱን ፡ ነው ፡ በዘመኔ ፡ ያየሁት

ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ ረዳት ፣ ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ አባት
ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ ፈዋሽ ፣ ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ ፍቅር
ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ ልዩ ፡ ነው ፣ ብለው ፡ አይበቃኝ ፡ ልዩ ነው

እርሱ ፡ ከሁሉም ፡ በላይ ፡ ነው
እርሱ ፡ ከሁሉም ፡ በላይ ፡ ነው
እርሱ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ ፡ ነው
እርሱ ፡ የአማልክት ፡ አምላክ ፡ ነው (፪x)