From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ህልምን ፡ ያሳየኸው ፡ ዮሴፍ ፡ ተጥሎ
ፍርድ ፡ ተጣሞበት ፡ በእስር ፡ ቤት ፡ ተረስቶ
አንተን ፡ የመጠበቅ ፡ ቢረዝምበት ፡ ጊዜው
ጠጅ ፡ አሳላፊው ፡ አታስበኝ ፡ አለው
ቀኑ ፡ ሲደርስ ፡ ግን ፡ በአንተ ፡ ተጐብኝቶ
በችኮላ ፡ ወጥቶ ፡ ጸሎቱ ፡ ተሰምቶ
ተለመነኝ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ተለመነኝ
ልመናዬ ፡ ወደ ፡ ጆሮህ ፡ ይድረስልኝ
ተለመነኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ተለመነኝ
ጸሎቴ ፡ ወደ ፡ ማደርያህ ፡ ይድረስልኝ(፪)
አቤቱ ፡ ልቤ ፡ ጨከነ(፬)
እግዚአብሔር ፡ አለቴ ፡ ኃይሌ ፡ ነው ፡ እያለ
ሰው ፡ ምን ፡ ያደርገኛል ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አለ
ልቤ ፡ ጨከነ
አቤቱ ፡ ልቤ ፡ ጽኑ ፡ ነው(፬)
በአምላኬ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ኃይሌን ፡ አድሳለሁ
ሰው ፡ ምን ፡ ያደርገኛል ፡ ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
ልቤ ፡ ጽኑ ፡ ነው
ፊትህን ፡ የሚሹ ፡ በእኔ ፡ አይነወሩ
ተስፋ ፡ የሚያደርጉህ ፡ አይተውኝ ፡ አይፈሩ
በምሕረትህ ፡ ፊትህ ፡ አርግልኝ ፡ ጌታዬ
ጉብኝትህ ፡ ይፍጠን ፡ በቤትህ ፡ በአገሬ
ፍጠንልኝ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ ፍጠንልኝ
እንደምሕረትህ ፡ ብዛት ፡ ፍረድልኝ
ፍጠንልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ ፡ ፍጠንልኝ
እንደኃጢአቴ ፡ ከቶ ፡ አታርግብኝ (፪x)
አበቱ ፡ ልቤ ፡ ጨከነ(፬)
እግዚአብሔር ፡ አለቴ ፡ ኃይለ ፡ ነው ፡ እያለ
ሰው ፡ ምን ፡ ያደርገኛል ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አለ
ልበ ፡ ጨከነ
አበቱ ፡ ልበ ፡ ጽኑ ፡ ነው(፬)
በአምላከ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ኃይለን ፡ አድሳለሁ
ሰው ፡ ምን ፡ ያደርገኛል ፡ ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
ልበ ፡ ጽኑ ፡ ነው
|