በእግዚአብሔር ፡ ዓለም (BeEgziabhier Alem) - ሳሙኤል ፡ ንጉሤ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ንጉሤ
(Samuel Negussie)

Samuel Negussie 1.jpg


(1)

በእግዚአብሔር ፡ ዓለም
(BeEgziabhier Alem)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2014)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ንጉሤ ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Negussie)

በዚህ ፡ ዓለም ፡ ምን ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ነገር ፡ አለ
ከአንተ ፡ ጋር ፡ አንደመኖር
በዚህ ፡ ምድር ፡ ምን ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ነገር ፡ አለ
ከአንተ ፡ ጋር ፡ አንደመኖር
እወደዋለሁ ፡ ሕይወቴን ፡ የለወጠው
እወደዋለሁ ፡ መኖሬን ፡ እወደዋለሁ

በአንተ ፡ ዘንድ ፡ ያለን ፡ የህይወት ፡ ቃል
ሌላ ፡ ስፍራ ፡ የትም ፡ ማላገኘው
ብር ፡ የማይሰጠኝ ፡ ወርቅ ፡ የማይሰጠኝ
የሕይወቴን ፡ አቅጣጫ ፡ የለወጠው

የሁልጊዜ ፡ ነው ፡ የልቤ ፡ ሰላም
ከመንፈስህ ፡ ከቃልህ ፡ የመነጨው
በዚህ ፡ አለም ፡ ነገር ፡ የማይወሰን
የእኔን ፡ ሕይወት ፡ የደስታ ፡ ያደረገው

ብዙ ፡ ደስታ ፡ አለ ፡ በሕይወቴ
ብዙ ፡ ሰላም ፡ አለ ፡ በሕይወቴ
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ስላለ
መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ በእኔ ፡ ውስጥ ፡ ስላለ

ሸክም ፡ የከበደው ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ይምጣ
ይረፍ ፡ ብለህ ፡ የጠራኸኝ ፡ አንተ ፡ እኮ ፡ ነህ
ሁሉንም ፡ ነገር ፡ ለ ፡ አንተ ፡ ሰጥቼ
እፎይ ፡ ብዬ ፡ ተደላድዬ ፡ ምኖርብህ

ኢየሱስ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ያለኝ ፡ ህብረት
ማለት ፡ ለእኔ ፡ አለሜ ፡ ነው
ለሕይወቴ ፡ ትርጉም ፡ ያገኘሁበት
ምክኒያቱ ፡ ነው ፡ የዘላለሜ ፡ የሰመረበት