እግዚአብሔር ሆይ እንዴት ድንቅ ነህ (Egziabher Hoy Endet Dink Neh) (Track 7) - ሳሙኤል ቦርሳሞ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ቦርሳሞ
(Samuel Borsamo)

Lyrics.jpg


(1)

እግዚአብሔር ሆይ እንዴት ድንቅ ነህ
((Egziabher Hoy Endet Dinq Neh))

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፬ (1992)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:44
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ቦርሳሞ ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Borsamo)

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እንዴት ፡ ድንቅ ፡ ነህ
ነፍሳችን ፡ ረካች ፡ በጉብኝትህ
ጥያቄያችንም ፡ ተመለሰልን
ስምህ ፡ ይባረክ ፡ ከፍ ፡ ይበልልን

ጠላት ፡ ጠፍሮ ፡ ፍፁም ፡ ተብትቦ
እንዳናመልክህ ፡ ዙሪያው ፡ ተክቦ
መሰንቆአችንን ፡ ከሰቀልንበት
ዛሬ ፡ አውርደን ፡ ንገሥ ፡ አልንበት

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እንዴት ፡ ድንቅ ፡ ነህ
ነፍሳችን ፡ ረካች ፡ በጉብኝትህ
ጥያቄያችንም ፡ ተመለሰልን
ስምህ ፡ ይባረክ ፡ ከፍ ፡ ይበልልን

እኛስ ፡ ቆዝመን ፡ አዝነንም ፡ ነበር
ማየት ፡ ተስኖን ፡ ከሞት ፡ ባሻገር
በትንሳኤው ፡ ኃያል ፡ ደስታን ፡ ሞልተኸን
በባዕድ ፡ ምድር ፡ እንዘምራለን

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እንዴት ፡ ድንቅ ፡ ነህ
ነፍሳችን ፡ ረካች ፡ በጉብኝትህ
ጥያቄያችንም ፡ ተመለሰልን
ስምህ ፡ ይባረክ ፡ ከፍ ፡ ይበልልን

ከአቻምና ፡ አምና ፡ ከአምናም ፡ ዘንድሮ
የአንተ ፡ ቸርነት ፡ ስንቱ ፡ ተቆጥሮ
ስንቱን ፡ ጨለማ ፡ አሸጋገርከን
ከምንገምተው ፡ በላይ ፡ ሆንክልን

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እንዴት ፡ ድንቅ ፡ ነህ
ነፍሳችን ፡ ረካች ፡ በጉብኝትህ
ጥያቄያችንም ፡ ተመለሰልን
ስምህ ፡ ይባረክ ፡ ከፍ ፡ ይበልልን