ተንቀን ፡ አንቀርም (Teneqen Anqerem) - ሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ
(Samuel Borsamo)

Lyrics.jpg


(2)

በጌታ ፡ ሁሉ ፡ ይቻላል
(Begieta Hulu Yechalal)

ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Borsamo)

 
ደስታችን ፡ በምድር ፡ ፍፁም ፡ ባይሆን ፡ እንኳን
ልባችን ፡ ሲመታ ፡ በመከራ ፡ ሃዘን
የጌታን ፡ መገለጥ ፡ በመጠበቃችን
የምንጽናናበት ፡ አዲስ ፡ አገር ፡ አለን

አዝ፦ ተንቀን ፡ አንቀርም ፡ ተጥለን ፡ በምድር
አዲስ ፡ አገር ፡ አለን ፡ ከአድማስ ፡ ባሻገር
ጌታም ፡ ይመለሳል ፡ ዳግም ፡ ሊያሳርፈን
በገዛ ፡ ዙፋኑ ፡ በቀኝ ፡ ሊያስቀምጠን

የምድር ፡ መጽዐተኛ ፡ ባለ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋ
በላይ ፡ ያለው ፡ ሽቶ ፡ በምድር ፡ የተገፋ
ባይደላውም ፡ እንኳን ፡ ፀንቶ ፡ በመታገስ
በክብር ፡ ያየዋል ፡ የናፈቀውን ፡ ንጉሥ

አዝ፦ ተንቀን ፡ አንቀርም ፡ ተጥለን ፡ በምድር
አዲስ ፡ አገር ፡ አለን ፡ ከአድማስ ፡ ባሻገር
ጌታም ፡ ይመለሳል ፡ ዳግም ፡ ሊያሳርፈን
በማያልፈው ፡ መንግሥት ፡ ዘለዓለም ፡ ሊያነግሰን

የዚህን ፡ ዓለም ፡ ሃሳብ ፡ ታግሎ ፡ ያሸነፈ
በመከራ ፡ ፀንቶ ፡ በትዕግሥት ፡ ያለፈ
አምላኩ ፡ ሲገለጥ ፡ እጅጉን ፡ ይፅናናል
ያልተሰማ ፡ ዜማን ፡ ውዳሴን ፡ ያፈልቃል

አዝ፦ ተንቀን ፡ አንቀርም ፡ ተጥለን ፡ በምድር
አዲስ ፡ አገር ፡ አለን ፡ ከአድማስ ፡ ባሻገር
ጌታም ፡ ይመለሳል ፡ ዳግም ፡ ሊያሳርፈን
በማያልፈው ፡ መንግሥት ፡ ዘለዓለም ፡ ሊያነግሰን

መከራም ፡ ይረሳል ፡ ሃዘንም ፡ ይቀራል
ያናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ ፡ እምባችንን ፡ ያብሳል
ጻድቅ ፡ ፈራጃችን ፡ በቅርብ ፡ ይገለጣል
የወጉትም ፡ ዐይኖች ፡ ፊት ፡ ለፊት ፡ ያዩታል

አዝ፦ ተንቀን ፡ አንቀርም ፡ ተጥለን ፡ በምድር
አዲስ ፡ አገር ፡ አለን ፡ ከአድማስ ፡ ባሻገር
ጌታም ፡ ይመለሳል ፡ ዳግም ፡ ሊያሳርፈን
በገዛ ፡ ዙፋኑ ፡ በቀኝ ፡ ሊያስቀምጠን (፪x)