ጌታ ፡ አበረታኝ (Geita Aberetagn) - ሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ
(Samuel Borsamo)

Lyrics.jpg


(2)

በጌታ ፡ ሁሉ ፡ ይቻላል
(Begieta Hulu Yechalal)

ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ቦርሳሞ ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Borsamo)

 
አዝ፦ ጌታ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ኢየሱስ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ፈጥኖ ፡ ደረሰና ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ
ነፍሴን ፡ ከሚዋጋ ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ

አሰላስላለሁ ፡ የጌታን ፡ በጐነት
በእኔ ፡ ላይ ፡ ያለውን ፡ የአላማውን ፡ ፅናት
ጌታ ፡ አስደንቆኛል ፡ አመስግን ፡ ይለኛል
ምህረቱን ፡ ልዘምር ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
ማዳኑን ፡ ልናገር ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
(፪x)

አዝ፦ ጌታ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ኢየሱስ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ፈጥኖ ፡ ደረሰና ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ
ነፍሴን ፡ ከሚዋጋ ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ

ሲጣሉ ፡ ብቻቸው ፡ ሲታዩ ፡ ግን ፡ በዙ
ከእሳት ፡ የሚታደግ ፡ ማን ፡ ይሆን ፡ ጐበዙ
የነገሥታት ፡ ንጉሥ ፡ የኃያላን ፡ ሃያል
በምስሉ ፡ ላይሰግዱ ፡ ከሚጨክኑት ፡ ጋር
ይቆማል ፡ እግዚአብሔር ፡ ስሙን ፡ ሊያስከብር
ጌታ ፡ አስደንቆኛል ፡ አመስግን ፡ ይለኛል
ምህረቱን ፡ ልዘምር ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
ማዳኑን ፡ ላወራ ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል

አዝ፦ ጌታ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ኢየሱስ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ፈጥኖ ፡ ደረሰና ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ
ነፍሴን ፡ ከሚዋጋ ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ

በአርጤክስስ ፡ ዘመን ፡ የሞት ፡ አዋጅ ፡ ወጣ
አይሁድ ፡ እንዲወገድ ፡ ዝክሩ ፡ እንዲታጣ
አዋጁን ፡ ለወጠው ፡ ሞትን ፡ ገለበጠው
ከላይ ፡ ተፈርዶበት ፡ ጽዋውን ፡ ጨለጠው
እግዚአብሔር ፡ ተዋጊ ፡ ስሙም ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው
ጌታ ፡ አስደንቆኛል ፡ አመስግን ፡ ይለኛል
ምህረቱን ፡ ልዘምር ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
ማዳኑን ፡ ልናገር ፡ በእርግጥ ፡ ይገባኛል
(፪x)

አዝ፦ ጌታ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ኢየሱስ ፡ አበረታኸኝ ፡ አጠገቤ ፡ ቆሞ
ፈጥኖ ፡ ደረሰና ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ
ነፍሴን ፡ ከሚዋጋ ፡ ከክፉ ፡ ፊት ፡ ቀድሞ