፫(3)
ነገሩ ፡ ተገለበጠ (Negeru Tegelebete)
፮ (6)
እግዚአብሔር ፡ ቸር (፫x) ምህረቱ ፡ ለዘለዓለም እውነቱም ፡ ለልጅ ፡ ልጅ ፡ ነውና ወደ ፡ ደጆቹ ፡ በመገዛት ፡ ኑና ወደ ፡ አደባባዮቹም ፡ ግቡ ፡ በምሥጋና ኑና ፡ ግቡ ፡ በምሥጋና ፀጋው ፡ ያዳናችሁ ፡ አመስግኑት ፍቅሩ ፡ የገባችሁ ፡ አመስግኑት ምህረቱን ፡ ተነጋገሩ ፀጋውን ፡ ተነጋገሩ ፍቅሩን ፡ ተነጋገሩ በማስተዋል ፡ ለእርሱ ፡ ዘምሩ ከሞት ፡ የወጣችሁ ፡ አመስግኑት ምህረቱን ፡ ያያችሁ ፡ አመስግኑት ተዓምራቱን ፡ ተነጋገሩ ጽድቁን ፡ ተነጋገሩ እውነቱን ፡ ተነጋገሩ በማስተዋል ፡ ለእርሱ ፡ ዘምሩ አባት ፡ የሆናችሁ ፡ አመስግኑት ጉያው ፡ ያሞቃችሁ ፡ አመስግኑት ቸርነቱን ፡ ተነጋገሩ ደግነቱን ፡ ተነጋገሩ አባትነቱን ፡ ተነጋገሩ በማስተዋል ፡ ለእርሱ ፡ ዘምሩ ሃሌሉያ (፬x) በሉ