የምትረዳ ፡ የምታስደግፍ (Yemetreda Yemetasdegef) - ነጻነት ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ነጻነት ፡ አሰፋ
(Netsanet Assefa)

Lyrics.jpg


(4)

አለኝ ፡ ብዙ ፡ ምሥጋና
(Alegn Bezu Mesgana)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:28
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የነጻነት ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Netsanet Assefa)

የምትረዳ ፡ የምትደግፍ ፡
 የምታጽናና ፡ የምታሳርፍ
 የማትለወጥ ፡ ሁሌ ፡ እውነተኛ
 አንተ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ ፡ ለኔ ፡ ጋደኛ
 ወዳጅ ፡ እንዳንት ፡ የለም
 ክብር ፡ ለዘለዓለም
 ወዳጅ ፡ እንዳንት ፡ የለም
 ክብር ፡ ለዘለዓለም

የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ የማጫውትህ
የእኔ ፡ ማረፍያ ፡ ወዳጄ ፡ እንተ ፡ ነህ
ይኸው ፡ በዘመኔ ፡ ይህንን ፡ አየሁ
እንዳተ ፡ የሚሆን ፡ አንዳችም ፡ አጣሁ
ይኸው ፡ በዘመኔ ፡ ይህንን ፡ አየሁ
እንዳተ ፡ የሚሆን ፡ አንዳችም ፡ አጣሁ
 ፡ማን ፡ ይተካል ፡ ታዲያ ፡ በአንተ ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ጌታ
 ፡ለማንም ፡ አልሰጥም ፡ የአንተን ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ

አዳኝነትህ ፡ ተመችቶኛል
በቀን ፡ በሌሊት ፡ ልቤ ፡ ያስብሃል
አትሰለችም ፡ ሁሌ ፡ ባወራህ
ልቤም ፡ ስለዚህ ፡ አንተን ፡ ፈለገህ
አትሰለችም ፡ ሁሌ ፡ ባወራህ
ልቤም ፡ ስለዚህ ፡ አንተን ፡ ፈለገህ
 ፡ማን ፡ ይተካል ፡ ታዲያ ፡ በአንተ ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ጌታ
 ፡ለማንም ፡ አልሰጥም ፡ የአንተን ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ

ከሃዘኔ ፡ ስታጽናናኝ
መከራዬንም ፡ ስታስረሳኝ
የልቤ ፡ ደስታ ፡ አንተ ፡ ስትሆን
ይህን ፡ አይቼ ፡ ወደድኩህ ፡ አንተን
የልቤ ፡ ደስታ ፡ አንተ ፡ ስትሆን
ይህን ፡ አይቼ ፡ ወደድኩህ ፡ አንተን
፡ማን ፡ ይተካል ፡ ታዲያ ፡ በአንተ ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ጌታ
 ፡ለማንም ፡ አልሰጥም ፡ የአንተን ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ

ልቤ ፡ እንደ ፡ ድንግል ፡ ይወድሃል
አንተን ፡ ሲያስብህ ፡ ደስ ፡ ይለዋል
የእኔ ፡ ሙሽራ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ
ፊትህን ፡ ሳይ ፡ ነው ፡ ፍጹ ፡ ደስታዬ
የእኔ ፡ ሙሽራ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ
ፊትህን ፡ ሳይ ፡ ነው ፡ ፍፁም ፡ ደስታዬ
 ፡ማን ፡ ይተካል ፡ ታዲያ ፡ በአንተ ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ጌታ
 ፡ለማንም ፡ አልሰጥም ፡ የአንተን ፡ ቦታ
 ፡ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ