አሳረፈኝ (Asarefegn) - ነጻነት ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ነጻነት ፡ አሰፋ
(Netsanet Assefa)

Lyrics.jpg


(4)

አለኝ ፡ ብዙ ፡ ምሥጋና
(Alegn Bezu Mesgana)

ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 6:50
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የነጻነት ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Netsanet Assefa)

የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
ጌታዬ ፡ አሳርፎኛል ፡
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
አሳርፎኛል

ሃሳቤን ፡ ሁሉ ፡ ወዲያ ፡ ትቼ
ለአላማህ ፡ ተነስቼ ፡
በጐነትክን ፡ ጽድቅህን ፡ ላውራ
አንተ ፡ አለህ ፡ ከኔ ፡ ጋራ
እንደኔማ ፡ እንደ ፡ ሃሳቤ ፡
አመስገኜ ፡ መች ፡ ጠገቤ
ከእንግዲህ ፡ የምኖረው
ለሞተልኝ ፡ ለእርሱ ፡ ነው

 ፡ ማን ፡ ነው ፡ ከእርሱ ፡ በቀር ፡ ነገን ፡ የሚያውቀው
 ፡ ትንፋሼን ፡ መንዴን ፡ እርሱ ፡ የያዘው
 ፡ እግዚአብሔር ፡ የሰራት ፡ ይህቺ ፡ ቀን ፡ ዛሬ ፡ ናት
 ፡ በእርሱ ፡ ደስ ፡ እያለኝ ፡ ሃሴት ፡ ላድርግባት ፡
 ፡ ግሩምና ፡ ድንቅ ፡ አድርጐ ፡ ፈጥሮኛል ፡
 ፡ በፈጥረኝ ፡ አምላክ ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
 ፡ ግሩምና ፡ ድንቅ ፡ አድርጐ ፡ ፈጥሮኛል ፡
 ፡ በፈጠረኝ ፡ ጌታ ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
 ፡ እኔ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በፈጣሪዬ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በመድሃኒቴ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኒ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ

የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
ጌታዬ ፡ አሳርፎኛል
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
አሳርፎኛል ፡


እርሱ ፡ ይሁን ፡ ብሎ ፡ በፈጠራቸው
እራሱ ፡ እይቶ ፡ መልካም ፡ ባላቸው
አምላኬ ፡ ፍቅሩ ፡ በዚህ ፡ አለበቃውም
የልቡን ፡ ሃሳብ ፡ አልገለጡትም
ፍቅሩን ፡ ለኔ ፡ እንዲህ ፡ ገለጠ ፡ ሃሃ
ራሱን ፡ መባ ፡ አድርጐ ፡ ስለኔ ፡ ሰጠ
አምላክ ፡ ሰው ፡ ሆኖ ፡ ምድር ፡ መጣና ፡ ሃሃ
የእርሱ ፡ አደርገኝ ፡ ሞተልኝና ፡
  
 ፡ እኔ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በፈጣሪዬ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በመድሃኒቴ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኒ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ

በፈቴ ፡ ያለውን ፡ ተራራ ፡ እያየሁኝ ፡
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ምን ፡ ተስፋ ፡ አስቆረጠኝ
ተራራን ፡ የሰራ ፡ ረዳቴ ፡ ይመጣና
መንገድ ፡ ያደርግልኛል ፡ ሜዳ ፡ ሁን ፡ ይልና
እርሱ ፡ አማኑኤል ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ መተከዝ ፡ ምንድ ፡ ነው
እርሱ ፡ አማኑኤል ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ መተከዝ ፡ ምንድ ፡ ነው
 
የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእኔ ፡ ነሽ ፡ ብሎ ፡ አሳረፈኝ
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
ጌታዬ ፡ አሳርፎኛል
የእርሱ ፡ አድሮጐኛል ፡
አሳርፎኛል ፡

ምህረት ፡ ቸርነቱን ፡ ፍቅሩን ፡ አይቻለሁ
ለሚታመኑበት ፡ መከታ ፡ ጋሻ ፡ ነው
አስተማማኝ ፡ አምባ ፡ እረኛ ፡ እርሱ ፡ ነው
መንጋዎቹን ፡ ከእጁ ፡ የማይነጠቀው
ደስ ፡ ይበለኝ ፡ እንዲ ፡ በዚህ ፡ ታላቅ ፡ ጌታ
ደስታን ፡ ባስታጠቀኝ ፡ በሰቆቃ ፡ ፈንታ
ሕይወትን ፡ በሰጠኝ ፡ ሞቶ ፡ በኔ ፡ ፈንታ ፡

 ፡ እኔ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በፈጣሪዬ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኔ ፡ በመድሃኒቴ ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ
 ፡ እኒ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ እሰኛለሁ