የኃያላን ፡ ኃያል (Yehayalan Hayal) - ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን
(Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

Lyrics.jpg


(1)

ብርሃን ፡ ወጣልኝ
(Berhan Wetalegn)

ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የናዝሬት ፡ አማኑኤል ፡ ሽብሸባ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Nazareth Amanuel Shebsheba Choir)

አዝ፦ የኃያላን ፡ ኃያል ፡ የዘለዓለም ፡ ጌታ
መልካም ፡ መዓዛ ፡ ያለው ፡ የሕይወት ፡ ሽታ
እናከብረዋለን ፡ ነፍሳችን ፡ ነቅታ (፪x)
ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው
ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው (፪x)

በላይ ፡ በሰማይ ፡ ለከበረው
እንደ ፡ በግ ፡ ለእኔ ፡ የታረደው
የናሱን ፡ ደጆች ፡ ለሰባበረው
ምሥጋና ፡ ክብር ፡ ውዳሴ ፡ ይድረሰው

አዝ፦ የኃያላን ፡ ኃያል ፡ የዘለዓለም ፡ ጌታ
መልካም ፡ መዓዛ ፡ ያለው ፡ የሕይወት ፡ ሽታ
እናከብረዋለን ፡ ነፍሳችን ፡ ነቅታ (፪x)

ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው (፪x)

ቆጥሬ ፡ የማልዘልቀው ፡ ውለታ ፡ አለብኝ
ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ የዋለልኝ
ምላሽ ፡ እንኳን ፡ ቢሆን ፡ በብዙ ፡ ጥቂት
ይኸው ፡ ምሥጋናዬ ፡ ወዳጄ ፡ ላለኸው ፡ በሰማይ

አዝ፦ የኃያላን ፡ ኃያል ፡ የዘለዓለም ፡ ጌታ
መልካም ፡ መዓዛ ፡ ያለው ፡ የሕይወት ፡ ሽታ
እናከብረዋለን ፡ ነፍሳችን ፡ ነቅታ (፪x)

ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው (፪x)

ውበቱ ፡ የሚያምር ፡ ማነው ፡ እንደ ፡ ውዴ
ግርማው ፡ የሚያስፈራ ፡ ማን ፡ እንደ ፡ ንጉሤ
ነገሥታት ፡ ኃያላን ፡ አለቆች ፡ በሙሉ
ግሩም ፡ ነው ፡ ድንቅ ፡ ነው ፡ እያሉ ፡ ለሥሙ ፡ ይገዛሉ

አዝ፦ የኃያላን ፡ ኃያል ፡ የዘለዓለም ፡ ጌታ
መልካም ፡ መዓዛ ፡ ያለው ፡ የሕይወት ፡ ሽታ
እናከብረዋለን ፡ ነፍሳችን ፡ ነቅታ (፪x)
ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው
ውዳችን ፡ ከእልፍ ፡ የተመረጠ ፡ ነው
ክበር ፡ ክበር ፡ እንበለው
ንገሥ ፡ ንገሥ ፡ እንበለው (፪x)