ሥምህን ፡ እዘምረዋለሁ (Semhen Ezemerewalehu) - መስከረም ፡ ጌቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስከረም ፡ ጌቱ
(Meskerem Getu)

Meskerem Getu 2.jpg


(2)

መንግሥትህ ፡ ትምጣ
(Mengesteh Temta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2016)
ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 5:05
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስከረም ፡ ጌቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Meskerem Getu)

አዝሥምህን ፡ እዘምረዋለው (፪x)
ዝናህን ፡ እዘምረዋለው
ሥምህን ፡ እዘምረዋለው
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ እላለሁ
ሥምህን ፡ እዘምረዋለው (፪x)
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ እላለሁ
አንተን ፡ እዘምርሃለው
ስላንተ ፡ መዝሙር ፡ እጽፋለው
ጌታ ፡ እዘምርሃለው
ሁልጊዜ ፡ ኢየሱስ ፡ እላለሁ

በጽድቅ ፡ መጠን ፡ እጅግ ፡ ከፍ ፡ ያልክ ፡ ነህ
ስምህ ፡ በምድር ፡ የተመሰገነ
ዝናህ ፡ ሁልጊዜ ፡ አስደናቂ ፡ ዜና
ወቅት ፡ የማይሽረው ፡ ዘላለም ፡ ገናና

አዝሥምህን ፡ እዘምረዋለው (፪x)
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ እላለሁ
ስላንተ ፡ ቆሜ ፡ አውጃለው
አንተን ፡ እዘምርሃለው
ስላንተ ፡ መዝሙር ፡ እጽፋለው
ጌታ ፡ እዘምርሃለው
በሥምህ ፡ ዜማ ፡ አወጣለው

ከቶ ፡ አይጨልምም ፡ በአንተ ፡ ፊት ፡ ጨለማ
ብርሃንነትህ ፡ ከጫፍ ፡ ጫፍ ፡ ይሰማ
ሞገስ ፡ ግርማህን ፡ ባውጅ ፡ ደጋግሜ
ቃሎች ፡ አነሱ ፡ የለህም ፡ ፍጻሜ

አዝሥምህን ፡ እዘምረዋለው (፪x)
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ እላለሁ
ስላንተ ፡ ቆሜ ፡ አውጃለው
አንተን ፡ እዘምርሃለው
ስላንተ ፡ መዝሙር ፡ እጽፋለው
ጌታ ፡ እዘምርሃለው
በሥምህ ፡ ዜማ ፡ አወጣለው

በሰማያት ፡ ያለኸው ፡ ልቀህ
በልቤ ፡ ላይ ፡ የተጻፍክ ፡ ደምቀህ
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ
ለዓለም ፡ ሁሉ ፡ ስምህን ፡ ላውጅ

ሃሌሉያ (፮x)