እግዚአብሔር ፡ ነህ (Egziabhier Neh) - መስከረም ፡ ጌቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስከረም ፡ ጌቱ
(Meskerem Getu)

Meskerem Getu 2.jpg


(2)

መንግሥትህ ፡ ትምጣ
(Mengesteh Temta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2016)
ቁጥር (Track):

፲ ፭ (15)

ርዝመት (Len.): 4:33
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስከረም ፡ ጌቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Meskerem Getu)

ልዑል ፡ አምላካችን ፡ እስኪ ፡ እንስገድልህ
የሚያክልህ ፡ የለም ፡ በግርማም ፡ በኃይልህ
ሥልጣናት ፡ አለቆች ፡ ለአንተ ፡ ተገዙ
ውበትህን ፡ አይተው ፡ በግርማህ ፡ ፈዘዙ

አዝ፦ ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አምላካችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ ፈጣሪያችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
ለእርስትህ ፡ መረጥከን ፡ ለየኸን
ሕዝቦችህ ፡ አደረግከን
፡ (፪x)


ምድርን ፡ በኃይልህ ፡ የፈጠርክ
ዓለምን ፡ በጥበብህ ፡ መሠረትክ
ሰማያትን ፡ በማስተዋል ፡ የዘረጋህ
አምሳያ ፡ የለህም ፡ ከአንተ ፡ ሚጠጋ
(፪x)

አዝ፦ ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አምላካችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ ፈጣሪያችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
  ለእርስትህ ፡ መረጥከን ፡ ለየኸን
ሕዝቦችህ ፡ አደረግከን
፡ (፪x)

ልዑል ፡ አምላካችን ፡ እስኪ ፡ እንስገድልህ
የሚያክልህ ፡ የለም ፡ በግርማም ፡ በኃይልህ
ሥልጣናት ፡ አለቆች ፡ ለአንተ ፡ ተገዙ
ውበትህን ፡ አይተው ፡ በግርማህ ፡ ፈዘዙ

አዝ፦ ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አምላካችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ ፈጣሪያችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
  ለእርስትህ ፡ መረጥከን ፡ ለየኸን
 ሕዝቦችህ ፡ አደረግከን
፡ (፪x)

ዙፋንህ ፡ ጽኑ ፡ ማይነቃነቅ
ዓመትህ ፡ ተቆጥሮ ፡ የማያልቅ
ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል ፡ ኃያል ፡ ግሩም ፡ ብርቱ
የጠቢባን ፡ ጥበብ ፡ በፊትህ ፡ ነው ፡ ከንቱ

አዝ፦ ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ አምላካችን ፡ ነህ
         ኦሆ ፡ ፈጣሪያችን ፡ ነህ
        ኦሆ ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ